የዳውሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት የአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክት አሕጽሮት

የዳውሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት የአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክት አሕጽሮት

የፕሮጀክቱ ቦታ ፦ የዳው ኮንታ ሀገረ ስብከት ስርስድስት ወረዳ ቤተክህነቶች ሲገኙ የአብነት ትምህርት ቤት ግንባታው የሚካሄደው የሃገረስብከቱ መቀመጫ በሆነው በተርጫ ከተማ ላይ በሚገኘው በአቡነ ተክለሃይማኖት ደብር ላይ ነው፡፡

ፕሮጀክቱ ማቋቋም ያስፈለገበት ምክንያት፦ ሀገረስብከቱ በመናፍቃን የተከበበ እና ጥቂት የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች ብቻ ያሉበት ከመሆኑም በላይ አገልጋይ ካህናት ሆኑ ዲያቆናት የሚመጡት ከሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በመሆኑ፣ እነዚህ አገልጋዮች ከአካባቢው ነዋሪ ጋር በቋንቋ መግባባት ስለማይችሉ ከቤተክርስቲያን አገልግሎት ውጪ የሃይማኖት ትምህርት መስጠት ባለ መቻላቸው ምዕመኑን ለማስተማር እና ሃይማኖቱን ጠብቆ እንዲኖር ማድረግ አልተቻለም፡፡ ስለዚህ በሀገረ ስብከቱ ላይ የሚቋቋመው የአብነት ትምህርት ቤት ተማሪዎቹ ተመልምለው የሚገቡት ከሁሉም ወረዳ ቤተክህነቶች ስለሚሆን ተምረው ሲጨርሱም ወደ መጡበት አካባቢ ተመልሰው ምዕመኑን በቅስና እና በድቁና ከማገልገላቸውም በላይ በሚገባው ቋንቋ የወንጌል ትምህርት ሊሰጡት ስለሚችሉ በሃይማኖቱ ፀንቶ እንዲኖር የሚኖራቸው አስተዋፅዖ ከፍተኛ ይሆናል፡፡

የፕሮጀክቱ ግብ ፦ በሀገረስብከቱ የአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ በማካሄድ የቤተክርስቲያን ካህናት እና ዲያቆናት በማፍራት የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት እንዲከፈቱ እና መንፈሳዊ አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ እንዲሰጡ ማድረግ ሲሆን፤ የፕሮጀክቱ ዓላማ በየሁለት ዓመት ግብረ ድቁና ተምረው የሚያጠናቅቁ 40 የአብነት ትምህርት ተማሪዎችን ተቀብሎ የአብነት ትምህርት ማስተማር የሚያስችል የአብነት ትምህርት ቤት መገንባት እና ከአብነት ትምህርቱ ጎን ለጎን መሰረታዊ ትምህርተ ሐይማኖት ትምህርት እና የስብከት ዘዴን ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ ነው፡፡

የአብነት ትምህርት ቤቱ ግንባታ የሚያጠቃልለው፦ ለ40 ተማሪዎች የሚሆን አንድ ጉባኤ ቤት፤ አምስት የተማሪዎች ማደሪያ፣ መመገቢያ አዳራሽ፣ ማብሰያ ቤት ፣ የመጸዳጃ እና ገላ መታጠቢያ ቤቶችን ነው፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞም ፕሮጀክቱ የውስጥ ቁሳቁስ ግዢንም ያጠቃልላል፡፡

ለፕሮጀክቱ የገንዘብ ምንጭ ፦ በአውሮጳ የሚገኙ ምእመናን፤ የአብነት ትምህርት ቤቱ ግንባታ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚታሰብ ሲሆን፣ የሚፈጀውም የገንዘብ  ብር 2,500,000 ብር (62, 500 EUR ) ይሆናል፡፡

የፕሮጀክቱ አስፈፃሚ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት እና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት ማስተባበሪያ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ ከተጠናቀቀ በኃላ በባለቤትነት ተረክቦ ለተፈለገው አገልግሎት እንዲውል የሚያደርገው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዳውሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት ይሆናል፡፡

ፕሮጀክቱ በታለመለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ተባባሪ የሚሆኑት፤ የፕሮጀክቱ ባለቤት የሆነው የዳውሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት፣ የአካባቢው ወረዳ ቤተክህነት፣ በማኅበረ ቅዱሳን የተርጫ ማዕከል፣ በአውሮጳ የሚኖሩ በጎ አድራጊ ምዕመናን እና የተለያዩ መንፈሳዊ ማኅበራት ይሆናሉ፡፡

ለገዳማት እና አብነት ት/ቤቶች ድጋፉ ለማድረግ የሚከተሉትን ዘዴዎች ይጠቀሙ  :-

  1. በቀጥታ በባንክ ወደ ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል ሂሳብ በማስተላለፍ

Mahibere Kidusan In Europa

BAN : DE14 3704 0044 0307 803 700

BIC : COBADEFF

Reason : Donation gedamate code 001

Commercial Bank

Bank address : Maternusstr.5; 50996 Cologne, Germany

 

  1. ፔይ ፓልን በመጠቀም ወደ አውሮፓ ማዕከል ባንክ አካውንት በማስተላለፍ።

ለተጨማሪ መረጃ እና ጥያቄ በ eu.monasteries@eotcmk.org ይጻፉልን።