የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ከሀገረ ዴንማርክ(ኮፐንሃገን) ወደ ሀገረ ስዊድን (ሉንድ)

ከዴንማርክ ኮፐንሃገን ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን በመነሳት ወደ ስዊድን፣ ሉንድ ደብረምጥማቅ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ነሐሴ 16/2013 . (Aug.22/2021) የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ተካሄደ።

ሐዊረ ሕይወቱን ያዘጋጅው የዴንማርክ ግንኝነት ጣቢያ ከደ/// አማኑኤል እና ከሉንድ /// ማርያም /ሰበካ ጉባኤያት ጋር በመተባበር ነው። በዚህ መርሐ ግብር ላይ የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ምእመናን እናበአጎራባች የሚገኙ አጥቢያዎች፣ አጠቃላይ 200 በላይ የሚሆኑ ምእመናን ተሳተፈዋል። የሁለቱም አጥቢያዎችአስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ደሬሳ፥ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ኃይለ ማርያም አያሌው እናመልአከ መዊእ ቀሲስ ሃይለ ጊዮርጊስ አሰፋ ተገኝተው ቃለ እግዚአብሔር እና ምክር ሰጥተዋል።  

መርሐ ግብሩ እሐድ ጠዋት 06:00 ላይ ከኮፐሃገን ///አማኑኤል ቤተክርስቲያን በመነሳት ወደ ሉንድ /// ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተደርጓል። በደብረ ምጥማቅም የኪዳን ጸሎት፥ የቅዳሴ ጸሎት በኋላ የሐዊረ ሕይወቱየመጀመሪያው ክፍል በጸሎተ ወንጌል ተጀምሮ በኮፐንሃገን የተስፋ ምሕረት //ቤት ዘማሪያን ያሬዳዊዝማሬያት እና የበገና መዝሙር አቅርበዋል።

ከዚያ በማስቀጠል በመልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤልከመረጥኹት፣ጋራ ቃል ኪዳኔን አደረግኹ መዝ883″ በሚል ርእስ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል። በማያያዝም የደ/ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንየአጥቢያው ምእመናን 30 ዓመታት በላይ ይጠቀሙበት የነበረውን ሕንጻ ኮንትራት፣ ለቀጣይ 100 ዓመታትመራዘሙን ምክንያት በማድረግ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ለሰጡት የስዊድን ቤተክርስቲያን እና ላስተባበሩትየሰብካ ጉባኤ አባላት ምስጋና በማቅረብ ሊሠራ ስለታቀደው ደጀ ሰላም ገለጻ ተደርጓል፡፡ ደጀ ሰላሙ በአውሮፓያሉ ምእመናን በፍልሰታና በሌሎች ጊዜያት መጥተው ሱባኤ ሊይዙበት የሚችሉ በመሆኑ እቅዱ እንዲሳካየምእመናን ሁለንተናዊ ትብብር እንዲደረግለት ሰበካ ጉባኤው ጥሪውን አስተላልፏል።  


የሐዊረ
ሕይወት 2 ክፍል የሆነው ምክረ አበው  በመጋቢ ሃይማኖት ቀሲስ ሃይለ ማርያም እና በመልአከ መዊእቀሲስ ሃይለ ጊዮርጊስ አማካኝነት 2ሰዓት ያክል ተከናውኗል። በምክረ አበውም ምእመናን ጥሩ ግንዛቤአግኝተውበታል። በተጨማሪም  የተስፋ ምሕረት / ተማሪዎች የተለያዪ ሥነ ጹሑፎችን በኅብረት አቅርበዋል።

በመጨረሻም ሰለ ማኅበረ ቅዱሳን ማንነት፥ ሰለአመሠራረቱ እና ስለሚከናውናቸው መንፈሳዊ መርሐ ግብራትከተገለጸ በኋላ፣ ይህን ሐዊረ ሕይወት በማዘጋጀት ለተሳትፉ ባለድርሻ አካላት ሁሉ በእግዚአብሔር ስም ምስጋናበማቅረብ በደ/// ማርያም ቤተ ክርስቲያን አውደ ምሕረት ውስጥ የነበረው መርሐ ግብር ተጠናቋል፡፡ ሐዊረሕይወቱ የዴንማርክ /// አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን አባላት ከሉንድ ///ማርያም ቤተክርስቲያን ወደኮፐንሃገን //ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ባደረጉት በዝማሬ የታጀበ የመልስ ጉዞ ተፈጽሟል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

በእንግሊዝ ሀገር የቨርችዋል ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ተመረቁ

ከዩኬ ንዑስ ማእከል 

ነሐሴ ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም

ተመራቂ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች (በከፊል) ከአባቶች ጋር

በማኅበረ ቅዱሳን አዉሮፓ ማእከል በዩናይትድ ኪንግደም ን/ማእከል አስተባባሪነት ላለፉት ሦስት ዓመታት ተከታታይ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሲማሩ የነበሩ 11 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ሐምሌ 24 ቀን 2013 ዓ/ም በአባቶች ቡራኬ ተመረቁ። በለንደን ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ በተካሄደዉ በዚህ የተማሪዎች ምርቃት መርሐ ግብር ላይ ካህናት አባቶች፣ ተመራቂ ተማሪዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች፣ ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች፣ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት፣ ሌሎች የግቢ ጉባኤ እንዲሁም የሰ/ት/ቤት ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን ሌሎች የአዉሮፓ ማእከል አባላት እና ታዳሚዎች መርሐ ግብሩን በዙም (Zoom) ተከታትለዋል። የአዉሮፓ ማእከል ሰብሳቢ ዲ/ን ፈንታ ጌቴ ለተመራቂዎች የ’እንኳን ደስ ያላችሁ’ መልእክት አስተላልፈዋል። በዚህም ተመራቂዎች ወደ ማኅበረ ቅዱሳን ተቀላቅለዉ የማኅበሩን አገልግሎት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል።

ትምህርት በመልአከ ሰላም ቀሲስ አዲስ ሲሰጥ

በዚህ የምረቃ መርሐ ግብር ላይ፣ መልአከ ሰላም ቀሲስ አዲስ አበበ የለንደን ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የስብከተ ወንጌል ኃላፊ ትምህርት ሰጥተዋል። በተጨማሪም ተማራቂዎችና የፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ተማሪዎች መዝሙር ያቀረቡ ሲሆን በግቢ ጉባኤ በመምህርነት ከሚያገለግሉት አባቶች መካከል መልአከ ሣህል ቀሲስ ዶ/ር ያብባል ሙሉዓለም እና ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ፍስሐ ለተመራቂዎች መልእክት አስተላልፈዋል።

 

ለተመራቂዎች የመስቀል ስጦታ በአባቶች ሲሰጥ

 

ለተመራቂዎች የመስቀል ስጦታ በአባቶች አማካኝነት ተበርክቷል። በን/ማእከሉ የተተኪ ትዉልድ እና ግቢ ጉባኤ ክፍል ተወካይ ለመርሐ ግብሩ ታዳሚዎች መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በዚህም ለግቢ ጉባኤዉ ስኬት አስተዋጽኦ ያደረጉትን መምህራንና ሌሎች አካላትን በሙሉ አመስግነዋል። ለምረቃ መርሐ ግብሩ የቤተ ክርስቲያኑን አዳራሽ ለፈቀደው የቤተ ክርስቲያኒቱ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ምስጋናቸዉን አቅርበዋል።

የተተኪ ትዉልድ ንዑስ ክፍል ባለፈዉ ዓመት ዕድሜያቸዉ ሰባት ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ከሦስት መቶ በላይ የሚደርሱ ህጻናትን፣ በየዕድሜያቸዉ ለይቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በእንግሊዘኛ ቋንቋ ሲሰጥ መቆየቱን አስታዉሰዉ ትምህርቱን በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በግቢ ጉባኤ ንዑስ ክፍልም እንዲሁ አዳዲስ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎችን ለመመዝገብ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጸዉ ይህንን የምዝገባ መልእክት በማስተላለፍ ሁሉም አካላት እንዲተባበሩ ጠይቀዋል።

የ’ቨርችዋል’ ግቢ ጉባኤዉ በዩኬ በመጀመሩ ምክንያት የዘንድሮ ተመራቂዎች ሁሉም ከዩኬ ሲሆኑ፣ ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ፣ ግቢ ጉባኤዉ በሌሎች የአዉሮፓ አገሮች ያሉ ተማሪዎችን ያካተተ በመሆኑ አሁን ላይ ወደ አዉሮፓ ግቢ ጉባኤነት ያደገ መሆኑን ገልጸዋል።

ግብረ-እስጢፋኖስ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማዕከል ግብረ-እስጢፋኖስ የተሰኘ ልዩ የዲያቆናት መርሐ ግብር በመጋቢት 23 እና 24፣ 2012 ዓ.ም አዘጋጀ፡፡

በማዕከሉ ትምህርት ክፍል አስተባባሪነት የተካሄደው ይህ መርሐ ግብር በአውሮፓ የሚኖሩ ዲያቆናትን በአንድ ላይ በማሰባሰብ ዲያቆናት ከቤተ መቅደስ አገልግሎት ጀምሮ ምዕመናንን በስብከተ ወንጌል በማስተማር ወንጌልን ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት የላቀ ሚና እንዲኖራቸው ለማደረግ ያለመ ነበር፡፡ በመርሐ ግብሩም የኢጣልያንና አካባቢው ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ ለዲያቆናት ትምህርት፣ ተግሳጽ፣ ቡራኬ፣ እና ቃለ ምዕዳን የሰጡ ሲሆን ካህናት አባቶች መነኮሳት እና በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት የሚገኙ ከ 40 በላይ የሚሆኑ ወንድሞች ዲያቆናት ተሳትፈዋል፡፡ ለሁለት ቀን የተካሄደው ይህ ልዩ የዲያቆናት መርሐ ግብር የሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስን ታሪክ፣ አገልግሎት በመዘከር እና ከሰማዕቱ እኛ ምን እንማራለን? የሚለውን ነጥብ ለተሳታፊዎች በማስገንዘብ ተጀምሯል፡፡ የክህነትን ሥርዓት እና ክብር በተመለከተ ትምህርት፣ ምክር በብጹዕ አቡ ሕርያቆስ የተሰጠ ሲሆን በቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ዶ/ር) አማካኝነት ደግሞ ሰፊ የክህነት ምንነት የግንዛቤ ማብራሪያ በማድረግ የመጀመሪያ ቀን መርሐ ግበር ተጠናቋል፡፡

  

በሁለተኛው ቀን በነበረው ቆይታም የስብከተ ወንጌልን ትርጉም እና አስፈላጊነት፣ ስብከተ ወንጌል እንዴት መቼ እና የት? መካሄድ አለበት የሚለውን በተመለከተ በመልአከ ሳህል ቀሲስ ያብባል ሙሉዓለም (ዶ/ር) አማካኝነት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ዲያቆናት በስብከተ ወንጌል አገልግሎት እንዳይሳተፉ የሚያደርጉ ችግሮችን ለመለየት በተሳታፊዎች መካካል ውይይት የተደረገ ሲሆን፦ በቂ የሆነ የመንፈሳዊ ዕውቀት አለመኖር፣ እራስን መደበቅ፣ ያልተገባ ፍርሃት፣ ስብከተ ወንጌልን መሠረት ያደረጉ የስልጠና ማዕከላትም ሆነ የመንፈሳዊ ኮሌጆች አለመኖር፣ እንዲሁም በአብነት ትምህርት ቤቶች ስብከተ ወንጌልን መሠረት ያደረገ የትምህርት እና የስልጠና ሥርዓት አለመኖሩ ከአብነት ትመህርቱ ጎን ለጎን የስብከተ ወንጌል ዲያቆናት ክህሎታቸውን እንዳያዳብሩ ያደረጓቸው ዐበይት ችግሮች መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡ 

በመጨረሻም ወንድሞች ዲያቆናት እነዚህን ችግሮች ተቋቁመው በክህነት አገልግሎት ኃለፊነታቸውን እንዲወጡ ታታሪዎች፣ አንባቢዎች እና ሁሌም በጸሎት የሚተጉ መሆን እንደሚገባቸው መልአከ ምሕረት አባ ዘሚካኤል ደሬሳ ምክራቸውን እና ተሞክሯቸውን በማካፈል እንዲህ አይነቱ መርሐ ግብር ወደፊት በሰፊ ሁኔታ መተግበር እንዳለበት በማሳሰብ ስልጠናው በጸሎት ተፈጽሟል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር።

አሜን፡፡

ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል

የኃዘን መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል: የታላቋ ብሪታኒያና የአየርላንድ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ዕረፍት የተሰማንን ኃዘን እንገልጻን፡፡
የብጹዕነታቸው በረከት ይድረሰን እያልን፡ በተለየ ሁኔታም ለአህጉረ ስብከቱ ሠራተኞች እንዲሁም ምእመናን የቤተ ክርስቲያን አምላክ መጽናናትን እንዲያድለን እንመኛለን፡፡

በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል

በቱሉዝ ፈረንሳይ የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ፡፡

በቀሲስ አለባቸው በላይ ከፈረንሳይ ግንኙነት ጣቢያ  

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ን የኢጣልያና አካባቢው ሀ/ስብከት በደቡብ ፈረንሳይ ቱሉዝ ከተማ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በተገኙበት ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ፡፡ ወደ አጥቢያ ቤተክርስቲያንነት ከማደጉ በፊት ‘የቱሉዝና አካባቢው ቅዱስ ሚካኤል ማኅበር’ በሚል ስያሜ የቆየ ሲሆን፤ አመሠራረቱም በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም አሁን ነዋሪነቱን በአሜሪካን ሀገር ያደረገ ዶ/ር ኢንጅነር ኃይሉ በላይ የሚባል የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ለወራት ሥልጠና ወደ ከተማዋ በመጣበት አጋጣሚ ኢትዮጵያዊያንን ፈልጎ በማግኘትና በማስተባበር ነበር፡፡ ከ2 ወራት በኋላ ኅዳር ወር 2008 ዓ.ም ከፓሪስ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ወልደ ትንሳኤን በማምጣት የመጀመሪያው የቅዳሴ አገልግሎት ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪም ክፍላትን በማዋቀር ማኅበሩ ቅርፅ እንዲኖረው የተደረገ ሲሆን፤ ከማኅበረ ቅዱሳን የፈረንሳይ ግንኙነት ጣቢያ ጋር በመተባበር ለአገልጋዮችም ተከታታይ ሥልጠናዎችን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች በመስጠት አቅም የማጎልበት ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ ላለፉት አራት ዓመታት በየወሩ የቅዳሴ አገለግሎት በማከናወን፣ ሕጻናትን ክርስትና በማንሳት፣ ብዙ ምእመናን የምስጢራት ተካፋይ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ለሀ/ስብከቱ በማሳየት በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ መልካም ፈቃድ በቀን 15/06/2012 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል ጽላት ገብቶ ማኅበሩ ወደ ቤተ ክርስቲያነት አድጓል፡፡  

C:\Users\User\Desktop\Mk France\Toulouse MMI\2020\87499442_679588912812286_2812710353425661952_n.jpg

በበዓሉ ዋዜማ ብዙ ቁጥር ያላቸው ምእመናን እና ካህናት ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በቱሉዝ (Blagnac) ኤርፖርት ተገኝተው ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ በብክብረ በዓሉ የማኅሌት፣ የትምህርትና እንዲሁም የቅዳሴ አገልግሎት በሊቀ ጳጳሱ መሪነት ተከናውኗል፡፡ ከቅዳሴ በኋላ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ “አስቀድማችሁ መንግስቱንና ጽድቁን ፈልጉ” (ማቴ6፡33) በሚል ርዕስ መነሻነት በሰጡት ሰፋ ያለ ትምህርት፤ የምእመናኑን መጠናከርና እዚህ ደረጃ መድረስ በማውሳት በቀጣይም ለበለጠእ የጽድቅ ሥራ መበርታት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ በመጨረሻም ተተኪን ከማፍራት እና የተደራጀ አገልግሎት ከመፈጸም አንጻር በኖርዌይ እሳቸው በበላይ ጠባቂነት የሚመሩትን ደብር ተሞክሮ አነስተው፤ ተተኪ ካህናትን ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም በብፁዕነታቸው ጸሎተ ምዕዳን የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ 

C:\Users\User\Desktop\Mk France\Toulouse MMI\2020\87570752_199724234680697_4328006035571736576_n.jpg


ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

በጀርመን ካስል ደብረ ቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስትያን ዐውደ ርዕይ ተካሄደ

በጀርመን ንዑስ ማእከል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማእከል የጀርመን ንዑስ ማእከል አዘጋጅነት “ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን አስተምህሮዋን እንጠንቅቅ፤ ድርሻችንን እንወቅ” በሚል መሪ ቃል የካቲት 22 ቀን 2012 ዓ.ም. በካስል ደብረ ቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ዐውደ ርዕይ ተካሄደ።

ዐውደ ርዕዩን የካስል ደብረ ቀራንዮ መድኃኔ ዓለም እና የሐምቡርግ ደብረ መድኃኒት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስትያን አስተዳዳሪ መጋቤ ምሥጢር ኅሩይ ኤርምያስ (ዶ/ር) በጸሎት የከፈቱት ሲሆን፤ ከ50 በላይ ምዕመናን ተመልክተውታል። ዐውደ ርእዩ በዋናነትም በአራት ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን ስለ ቤተክርስቲያናችን መሠረተ እምነት፣ ስለ ሐዋርያዊ አገልግሎት ምንነትና እና የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የሐዋርያዊ አገልግሎት ጉዞ፣ በዓለምና በኢትዮጵያ በተለያዩ ክፍላተ ዘመን ስለነበረው የቤተ ክርስቲያን ተጋድሎ፣ እና ወቅታዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተጋድሎ (በተለይም ከአክራሪ እስልምና ች እና ከፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ጋር ያለው ተጋድሎ) በድምጽ ወምስል የታገዘ ገለጻ በዝርዝር ቀርቧል፡፡ 

የጀርመን ንዑስ ማዕከልም ለዝግጅቱ መሳካት ከጅማሬ እስከ ፍጻሜ ከፍተኛ ትብብር ያደረጉትን የደብሩን አስተዳዳሪ እና ሰበካ ጉባኤ፣ በዐውደ ርእዩ ላይ በገላጭነት የተሳተፉትን የደብሩን ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፣ ለዝግጅቱ መሳካት በተለያየ መልኩ እገዛ ያደረጉትን ምዕመናን በሙሉ አመስግኖ ይህ ቀና ትብብር ለወደፊትም እንደማይለየው ያለውን ጽኑ እምነት ገልጿል። 

በመጨረሻም መጋቤ ምሥጢር ዶ/ር ኅሩይ ኤርምያስ ከምንጊዜውም በላይ ለቤተክርስቲያን ህልውና በጋራ የምንቆምበት ጊዜ በመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመደገፍ ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽዖ ልናደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተጨማሪም ደብሩ በአሁኑ ወቅት ያለበትን የሕንጻ ቤተክርስትያን ግዢ ዕዳ እንዳጠናቀቀ ማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚያደርገውን የገዳማት እና የአብነት ት/ቤቶችን ልማት እንቅስቃሴ በተለያዩ መንገዶች እንደሚደግፍ ቃል በመግባት መርሐ ግብሩን በጸሎት ዘግተዋል፡፡


በአውሮፓ ተወልደው ላደጉ የአብነት ተማሪዎች ሢመተ ዲቁና ተሰጠ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስዊድንና ስካንዴኒቪያን ሀገረ ስብከት የኦስሎ መካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በአውሮፓ ተወልደው ላደጉ ሰባት የአብነት ተማሪዎች ዲቁና ተሰጠ። 

ለ 4 ዓመታት የአብነት ትምህርታቸውን ሲከተታሉ ለነበሩት ሰባት አዳጊ የአብነት ተማሪዎች ኅዳር 28 ቀን 2012 ዓ.ም. በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብጹዕ አቡነ ኤልያስ ማዕርገ ዲቁና ተሰጥቷል፡፡ 

የኢጣሊያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስም እ.ኤ.አ ከ2015 ዓ.ም. ጀምሮ በደብሩ የአብነት ትምህርት ቤትን በማቋቋም፣ የአብነት ትምህርቱንም በማስተማር፤ ተተኪው ትውልድ በትክክል እንዲቀረጽ እና የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እንዲሆን፣ በደብሩ የሚገኙት አዳጊ ወጣቶችም በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በፍቅረ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዲያድጉና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ እንዲያውቋት በማድረግ ረገድ፡ በአጥቢያው የሚገኙትን ማኅበረ ምእመናን በማስተባበር አባታዊ ሓላፊነታቸውን በመወጣት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ 

በአሁኑ ጊዜ በደብሩ ከአንድ መቶ በላይ ተማሪዎች የአብነት ትምህርት በመከታተል ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ ሕጻናት እና ወጣት ሴቶችን ለማበረታታት መዝሙረ ዳዊት ላይ የደረሱ እንዲሁም ውዳሴ ማርያም በመጨረስ ላይ ያሉ ሁለት ሴት ተማሪዎች በብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ የተዘጋጀላቸውን የማበረታቻ ሥጦታ ከብጹዕ አቡነ ኤልያስ እጅ ተቀብለዋል። በተጨማሪም በዲቁና ሲያገለግሉ የነበሩ አንድ አገልጋይም በዕለቱ ማዕርገ ቅስና ተቀብለዋል፡፡

በማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል የኖርዌይ ንዑስ ማእከል አባላትም የአብነት ትምህርቱ እንዲጠናከር በማስተማር እና በማስተባበር የበኩላቸውን አስተዋጾ በማበርከት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

በፍራንክፈርት ከተማ ዐውደ ርእይ ተካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማእከል የጀርመን ንኡስ ማእከል አዘጋጅነት “ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን አስተምህሮዋን እንጠንቅቅ፤ ድርሻችንን እንወቅ” በሚል መሪ ቃል ኅዳር 28 ቀን 2012 ዓ.ም. በፍራንክፈርት ምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ዐውደ ርእይ ተካሄደ::

ዐውደ ርእዩን የጀርመን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅና የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ መዊዕ ልሳነ ወርቅ ውቤ በጸሎት የከፈቱት ሲሆን፤ የደብሩ ካህናት እና ከ100 በላይ ምዕመናን ተመልክተውታል። ዐውደ ርእዩ በዋናነትም በአራት ክፍሎች ተደራጅቶ፤ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መሠረተ እምነት፣ ስለ ሐዋርያዊ አገልግሎት ምንነትና እና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያዊ አገልግሎት ጉዞ፣ በዓለምና በኢትዮጵያ በተለያዩ ክፍላተ ዘመን ስለነበረው የቤተ ክርስቲያን ተጋድሎ፣ እና ወቅታዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተጋድሎ (በተለይም ከአክራሪዎች እና ከፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ጋር ያለው ተጋድሎ) በድምጽ ወምስል የታገዘ ገለጻ በዝርዝር ቀርቧል፡፡

በመጨረሻም ማኅበረ ቅዱሳን ባለፉት ዓመታት ውስጥ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የነበረውን የአግልግሎት ሱታፌ እና አስተዋጽኦ በተንቀሳቃሽ ምስል በታገዘ መልኩ የቀረበ ሲሆን የማኅበረ ቅዱሳን አመሠራረት፣ ርእይ፣ እና የአገልግሎት መስኮች እንዲሁም በአውሮፓ ማዕከል እና በጀርመን ንዑስ ማዕከል ስላለው እንቅስቃሴ በሊቀ ትጉኃን ቀሲስ አብርሃም አሰፋ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል፡፡ 

ዐውደ ርእዩን ከተመለከቱ ካህናት እና ምዕመናን ጋር ስለ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ፈተናዎች በተለይም እየከፋ ስለሄደው የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል፣ የምዕመናን መገደል እና መፈናቀል ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ በውይይቱ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎችም በሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ በመልአከ መዊዕ ቀሲስ ልሳነ ወርቅ ውቤ ማብራሪያ ተሰጥቷል። 

የጀርመን ንዑስ ማዕከልም ለዝግጅቱ መሳካት ከጅማሬ እስከ ፍጻሜ ከፍተኛ ትብብር ያደረጉትን የደብሩን አስተዳዳሪ እና ሰበካ ጉባኤ፣ ዐውደ ርእዩ ላይ በገላጭነት የተሳተፉትን የደብሩን ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፣ ለዝግጅቱ መሳካት በተለያየ መልኩ እገዛ ያደረጉትን እንዲሁም ረጅም ሰዓት ወስደው ዐውደ ርእዩን የጎብኙትን ምዕመናን በሙሉ አመስግኖ ይህ ቀና ትብብር ለወደፊትም እንደማይለየው ያለውን ጽኑ እምነት ገልጿል። 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ አንድነቷን መመለስ ተከትሎ፣ ማኅበረ ቅዱሳን በነበረው የአስተዳደር ልዩነት ምክንያት አገልግሎቱን ሳይሰጥ በቆየባቸው አጥቢያዎች አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ የማኅበረ ቅዱሳን ተወካይ መልአከ ሣህል ቀሲስ ያብባል ሙሉዓለም ገልጸዋል። ይህ ዐውደ ርእይም ማኅበረ ቅዱሳን ብዙ ካህናት እና ምዕመናን ባሉት፣ የራሱ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ባለቤት በሆነው፣ እንዲሁም ከሕጻናት እስከ አዋቂዎች ሰፊ አገልግሎት በሚሰጥበት በፍራንክፈርት ምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ያካሄደው የመጀመሪያ አገልግሎቱ ነው፡፡

በመጨረሻም መልአከ መዊዕ ቀሲስ ልሳነ ወርቅ ውቤ ዐውደ ርእዩ እንዲሳካ ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው ከምንጊዜውም በላይ ለቤተክርስቲያን ኅልውና በጋራ የምንቆምበት ጊዜ በመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመደገፍ ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽዖ ልናደርግ እንደሚገባ በማሳሰብ መርሐ ግብሩን በጸሎት ዘግተዋል፡፡


በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እየደረሰ ያለውን ጥቃት በመቃወም በተለያዩ የአውሮፓ አገራት ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ፡፡

መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ግዴታ ያለበት በመሆኑ በአገር ቤት በምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በልጆቿ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲያስቆም፣ አብያተ ክርስቲያነቱን ያቃጠሉ በልጆቿ ላይም ግፍን ያደረጉ ሰዎችን ለፍርድ እንዲያቀርብ ለመጠየቅ በአውሮፓ በሚገኙ ሦስቱ አህጉረ ስብከት (የስዊድንና የስካንዴኒቪያን ሀገረ ስብከት ፣ ጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት እና የጣልያንና አካባቢው ሀገረ ስብከት) አስተባባሪነት በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ  ተካሂዷል፡፡

ሰላማዊ ሰልፎቹ በ ጣልያን ሮም፣ ቤልጅየም ብራስልስ፣ ጀርመን በርሊን፣ ሆላንድ ዘሄግ፣ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ.፣ ስዊድን ስቶክሆልም እና በ ኦስትሪያ ቪዬና ኅዳር 26 ቀን 2012 ዓ.ም. ተካሄደዋል፡፡ በተጨማሪም በፈረንሳይ ፓሪስ ኅዳር 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ተካሂዷል፡፡ በሰልፎቹም ላይ የጀርመን እና አካባቢው አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ዲዮናስዮስ፣ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ፣ የየአድባራት አስተዳዳሪዎችና አገልጋይ ካህናት፣ የሰ/ት/ቤት ወጣቶች እና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በሌሎቹም አገራት የየአህጉረ ስብከት ተወካዮች፣ የየአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ካህናት፣ የሰ/ት/ቤት ወጣቶች እና ምእመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከናውኗል፡፡

ሰልፉ በሁሉም ሥፍራ በጸሎተ ወንጌል የተጀመረ ሲሆን፡ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እየደረሰ ያለው መገፋትን እግዚአብሔር እንዲመለከትም ጸሎተ ምሕላ ደርሷል፡፡ በሰልፉ ላይ የተገኙት አባቶችም “ጩኸታችንን ለዓለም ሕዝብ በማሰማት ብቻ እንዳይገታ ይልቁንም ከፊት ይልቅ ይበልጥ ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን እና እግዚአብሔርን ስለ ምትወድደው አገራችን በፍጹም ኀዘን ልናሳስብ ይገባል” በማለት መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ ሰላማዊ ሰልፎቹ የተካሄዱበት ዓላማም በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ለማውገዝ፣ እንዲቆም ለመጠየቅ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ሚዲያዎች ተገቢውን ሽፋን ሊሰጡት ስላልቻሉ የተለያዩ ሚዲያዎች እና የዓለሙ ማኅበረሰብ እንዲያውቀው እና ይህን ችግር እየፈጠሩ ያሉ አካላት ላይም ሆነ የኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጫና እንዲፈጥሩ ለማድረግ መሆኑን በሰልፉ ላይ የተገኙ አባቶችና አስተባባሪዎች ተናግረዋል፡፡

 በክርስቲያኖች ላይ የተቃጣውን ጥቃት የዓለሙ ማኅበረሰብ እንዲያውቀውና እንዲያወግዘው ለማድረግ ታስቦ የተደረገው ሰልፍ፡ በየአህጉረ ስብከቶቹ ሊቃነ ጳጳሳት በየሀገራቱ ቋንቋዎች የተጻፉት የአቤቱታ ደብዳቤዎች በሮማ ለፓርላማው ጽ/ቤት፣ በበርሊን ለጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ዴስክ፣ በጀርመን ለአውሮፓ ህብረት ጽ/ቤት፣ ለፈረንሳይ እና አሜሪካ ኢምባሲዎች፣ በዘሄግ ለኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ በስቶክሆልም ለስዊድን ገዢ ፓርቲ፣ በጽሑፍ ቀርበዋል፡፡ አባቶችና የምእመናን ተወካዮችም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የየሀገራቱ ተዋካዮች ጋር በመነጋገር ለተጨማሪ ውይይት ቀጠሮ ማስያዛቸው ታውቋል፡፡ በሆላንድም እንዲሁ የኢትዮጵያው አምባሰደር የሰልፉን ተወካዮች በቢሮአቸው በመቀበል አነጋግረዋቸዋል፡፡

በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከተላለፉት መልእክታት እና መፈክሮች መካከል ሀገር ከነድንበሩ፣ ነጻነትን ከነክብሩ፣ ፊደልን ከነቁጥሩ ያስረከበች ቅድስት ቤተክርስቲያን ይህ አይገባትም፤ የቤተ ክርስቲያን ጩኸትና አቤቱታ ይሰማ፤ አክራሪ ብሔርተኞችና ጽንፈኞች እጃቸውን ከቤተክርስቲያን ላይ ያንሡ፤ ቤተክርስቲያንን ያቃጠሉ፣ ካህናትንና ምዕመናንን የገደሉ በሕግ ይጠየቁልን፤ የሚሉ እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡

ሰልፉ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ በተያዘላቸው መርሐ ግብራት መሠረት የተከናወኑ ሲሆን፤ በሥራ ቀን የተደረገ ቢሆንም የተገኙት የምእመናን ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በሮም የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑና የ የታላቋ ብሪታንያ እና አየርላንድ ሀገረ ስብከትም ከወራት በፊት በተመሳሳይ መልኩ በለንደን ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉና በለንደን ከኢትዮጵያ ኢምባሲ ጋርም ውይይት ማካሄዱ ይታወሳል፡፡

ከየከተማዎቹ የተወጣጡ የተወሰኑ ፎቶዎች

ሮም ፤ ጣልያን
ጀርመን ፤ በርሊን
ስዊድን ፤ ስቶክሆልም
ሆላንድ ዘሄግ በ ኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ

፮ተኛው ሐዊረ ህይወት በጀርመን ሀገር ሆክስተር ከተማ ተካሄደ።

ሚያዚያ 17 ቀን 2011 ዓ.ም

በጀርመን ንዑስ ማዕከል

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤ/ማ/መ/ ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማዕከል የጀርመን ንዑስ ማዕከል ያዘጋጀው፥ ፮ተኛው ሐዊረ ህይወት በጀርመን -ከሃኖቨር  ከተማ 90 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ሆክስተር ከተማ በሚገኘው የግብጽ ኦርቶዶክስ ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ ማውሪስ ገዳም ከሚያዚያ ፬ እስከ ፮ ድረስ በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ።

ዓርብ ማምሻውን አባቶች ካህናት በተገኙበት በጸሎት ተከፍቶ፥ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ አብርሃም እንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አሰተላልፈዋል። በመቀጥልም ቀሲስ ግሩም ታየ የዕለቱን ትምህርት ካስተማሩ በኋላ፥ የእራት መስተንግዶ ተካሂዶ የምሽቱ መርሐ ግብር ተጠናቋል።

ቅዳሜ ጠዋት በቤተክርስቲያናችን ካህናትና ዲያቆናት ሥርዓተ ቅዳሴ የተፈጸመ ሲሆን፥ ከቅዳሴ በኋላ በነበረው የጠዋቱ መርሐግብር መክፈቻ ላይ የገዳሙ የበላይ ጠባቂ እና በግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሰሜን ጀርመን ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ደሚያን “እንኳን ወደ ገዳማችሁ በደህና መጣችሁ፤ በመምጣታችሁ ተደስቻለሁ በርቱ ጠንክሩ በነፍስም በሥጋም ጎልምሱ” በማለት መልእክት አስተላልፈዋል።

 

ለጉባዔው ከተዘጋጁት ዋና ትምህርቶች መካከል፥ “ነገረ እግዚአብሔር” በሚል ርዕስ በመጋቤ ምሥጢር ዶ/ር ኅሩይ ኤርምያስ ተሰጥቷል። መምህሩ ሀልዎተ እግዚአብሔርን በሚመለከት የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ፥ ከተለያዩ የፍልስፍና አስተምህሮዎች አንጻር በግልጽ አቀራረብ ያስተማሩ ሲሆን፥ በተጨማሪምየእግዚአብሔር ስሞችንና ባህርያት በሰፊው የዳሰሰና፥ ለተሳታፊዎች ብዙ ዕውቀትን ያስጨበጠ ትምህርት ነበር። 

በመቀጠልም መልአከ ስብሐት ተክሌ ሲራክ ከትምህርቱ ርዕስ ጋር የሚሄድ ያሬዳዊ ዜማ “አነ ቀዳማዊ ወአነ ደኃራዊ ይስማ ሰማይ ወታጽምእ ምድር” ትርጉሙም “መጀመሪያ እኔ ነኝ፥ መጨረሻም እኔ ነኝ ፤ ሰማይ ይስማ ምድርም ታድምጥ” ካቀረቡ በኋላ፥ ሊቃውንት ለሚያዚያ 5 አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓል ያዘጋጁትን የማኅሌት ዜማ አሰምተዋል።

የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ዋና ጸሐፊ ቆሞስ አባ ስብሐት ለአብ ሀገረ ስብከቱን ወክለው ባስተላለፉት መልእክት፥ ማኅበሩ እየሠራው ያለውን አገልግሎት አድንቀው፥ ሀገረ ስብከቱ እንደቀድሞው ማኅበሩ ቤተክርስቲያንን ለመደገፍ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በቅርበት ለመክታተል እና እገዛ ለማድረግ፥ እንዲሁም ማኅበሩ አገልግሎቱን ከሌሎች የሀገረ ስብከቱ ክፍሎች ጋር በቅንጅት እንዲያደርገው ፍላጎቱ እንደሆነ ገልጸዋል።

በመቀጠልም ከምዕመናን ለቀረቡ መንፈሳዊ ጥያቄዎች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን መልስ ከተሰጠ በኋላ፥ በንዑስ ማዕከሉ ሚድያ ክፍል የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ እንቅስቃሴ ዓላማ፥ ያለበት ደረጃ፥ ያሉት ተግዳሮቶች፥ የሚዲያ ሽፋኑ ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ጋር በንጽጽር የቀረበ ሲሆን፥ ከምዕመናን ምን አንደሚጠበቅም ጥናቱ ጠቁሟል።

በማስከተልም ለጉባዔው የተዘጋጀውን ትምህርት “ምሥጢረ ንስሐ” በሚል ርዕስ የሰጡት ቀሲስ ዶ/ር ያብባል ሙሉዓለም ናቸው። መምህሩ በተለይም በተሠራ ኃጢአት ከመጸጸት እና ከመመለስ በተጨማሪ ለካህን መናዘዝ የምሥጢረ ንስሐ ዋነኛው አካል መሆኑን ከመጽሐፍ ቅዱስ እና ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን እየጠቀሱ በሚገባ ያስረዱ ሲሆን፥ በተጨማሪም የቅዱሳንን የንስሐ ሕይወት አሁን እኛ ከምንኖረው ሕይወት ጋር በማዛመድ ዘመኑን የዋጀ ትምህርት ሰጥተዋል።

ሌላው በሐዊረ ህይወቱ ትኩረት የተሰጠው፥ በማኅበረ ቅዱሳን እየተካሄደ ያለውን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችና ተግዳሮቶች፥ እንዲሁም የምዕመናንና ማኅበራት ሚና ምን መምሰል እንዳለበት በዲ/ን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ ከቀረበ በሁዋላ ብዙሃንን በእንባ ያራጨው ከጉዳዩ ጋር ተያያዝነት ያለው የታየው ቪዲዮ ነው። ይህንንም ያዩ ካህናትና ምዕመናን እስካሁን ይህንን ነገር በደንብ ሳይገነዘቡ መቆየታቸው ምን ያህል እንደቆጫቸው ተናግረው፤ ከዚህ ቀን ጀምሮ ለታቀዱት ፕሮጀክቶች የተቻላቸውን እንደሚያበረክቱም ቃል ገብተዋል።

የቅዳሜ ፍጻሜ መርሐግብር የነበረው የገዳሙን ሙዚየም መጎብኘት ነው። ጉብኝቱም ታዳሚዎችን ያስተማረ ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ቅናት እንዲቃጠሉ ያደረገም ነበር።  ከዚህም መካከል በጀርመን የሚኖሩ ግብጻውያን ቁጥራቸው ከኢትዮጵያውያን የሚያንስ ሲሆን፥ ነገር ግን በጀርመን ሀገር ሁለት ትልልቅ ገዳማትን እና ሌሎች ተቋማትን መግዛት የቻሉበት ትጋት እና አርቆ አሳቢነት፥ እንዲሁም ገዳሙ ውስጥ የግብጽን ቤተክርስቲያን ታሪክ እና አስተምህሮ ለማስተዋወቅ በጀርመንኛ ቋንቋ ያዘጋጁት ቋሚ ዐውደ ርዕይ ወዘተ ተጠቃሽ ናቸው።    

በመጨረሻም እሁድ ጠዋት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ካህናትና ዲያቆናት በጋራ ሥርዓተ ቅዳሴ አካሂደው የ፮ተኛው ሐዊረ ህይወት መርሐ ግብር ፍጻሜ ሆኖዋል።

በመንፈሳዊ ጉባዔው ላይ ወደ 150 የሚጠጉ ምዕመናንና ህጻናት የተገኙ ሲሆን ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ሐዊረ ህይወት መርሐ ግብር ላይ ሲገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነና በነበረው ጉባዔ እጅግ እንደተደሰቱ፥ ብዙ መንፈሳዊ ትምህርቶችንና በቤተክርስቲያን እየተካሄዱ ስላሉ አገልግሎቶች ዕውቀት እንዳገኙ ተናግረዋል።

        

የጀርመን ንዑስ ማዕከል ከዚህ በፊት 5 ሐውረ ሕይወቶችን ፍራንክፈርት አካባቢ በሚገኘው ክሩፈልባህ ከተማ ባለው የቅዱስ እንጦን ገዳም ማድረጉ የሚታወስ ነው።