አቡነ መብዓ ጽዮን (በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን)

ጥቅምት ፳፭ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም

መብዓ ጽዮን በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ልጅ በማጣታቸው በጾምና በጸሎት ፈጣሪያቸውን ከሚለምኑ ባልና ሚስት ተወለዱ። የንቡረ እድ ሳሙኤል ረባን የሆነው መብዓ ጽዮን አባቱ እስከ ዳዊት ያለውን ትምርት አስተማረውና ዲቁናን ተቀበለ። ልጁ የትምህር ዝንባሌ እንዳለው አባቱ ተረድቶ ቤተ ማርያም ከሚባለው ደብር ወስዶ ተክለ አማኅ ከሚባል የቅኔ መም ዘንድ አስገባው። በዚያም ቅኔና እና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን እውቀቶችን ገበየ። ከዚህም በተጨማሪ ሥዕል መሳልና ጽሕፈት መጻፍ ተማረ። መብዓ ጽዮን የልጅነቱን ዘመን ሲፈጽም ‹‹ለነፍሳቸው ድኅነት ዋጋ ያገኙ ቅዱሳን ብዙ ናቸው።በመጾም ያገኙ አሉ፤ በትምርት ያገኙ አሉ፤ በድካም ያገኙ አሉ፤ በጸሎት በትጋት ያገኙ አሉ፤ እኔ ግን የጌታዬን የኢየሱስ ክርስቶስን የሞቱን መታሰቢያ ማድረግ ይገባኛል። በዚህም ፊቱን አያለሁ፤ እርሱ ጌታ ለደቀመዛሙርቱ ‹‹የትንሣኤዬን መታሰቢያ ብታደርጉ የሞቴን መታሰቢያ አድርጉ›› ብሏልና›› በማለት ፍላጎቱ በምንኩስና በመኖር ፈጣሪን ማገልገል መሆኑን ለወላጆቹ ገለጸላቸው።

Read more

አብርሃ ወአጽብሐ

ጥቅምት ፭ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም

ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሐ አባታቸው ታዜር እናታቸው ሶፍያ/አህየዋ/ በቅድስና የሚኖሩ እግዚአብሔርን በቅድስና በንጽህና የሚያገለግሉ ነገር ግን ልጅ ያላገኙ መካኖች ነበሩ። ስለሆነም ጌታ ሆይ ደስ የሚያሰኝህ በትእዛዝህም የሚኖር ልጅ ስጠን እያሉ እግዚአብሔርን ይለምኑ ነበር፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ስለ እግዚአብሔር ቸርነት ሲነጋገሩ ንግሥት ሶፍያ የሐና እመ ሳሙኤልን ጸሎት በመጥቀስ እሷም እንደ ሐና ሱባዔ ገብታ ፈጣሪዋን እንድትለምን ንጉሡን ጠየቀችው፤ ንጉሡም ኦ ብእሲቶ ሰናየ ሀለይኪ- አንቺ ሆይ መልካም አስበሻል በማለት በምክሯ ተስማምቶ ሱባዔ ገብታ ፈጣሪዋን በጸሎት እንድትጠይቅ ፈቀደላት፡፡ ንግሥት ሶፍያም የካቲት 18 ቀን ሱባዔ ገብታ ፈጣሪዋን መለመን ጀመረች፡፡ ከጸሎቷም ጥቂቱ «በኪሩቤል ላይ የምትኖር፣ ቀለያትንም (ጥልቅ ባሕርንም) የምትመለከት ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ አቤቱ ጸሎቴንና ልመናዬን ስማኝ፤ ልቅሶየንም አድምጥ ቸል አትበለኝ» የሚል ነበር፡፡

Read more

አብርሃ ወአጽብሐ

ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም

ቅዱሳን ነገስታት አብርሃ ወአጽብሐ አባታቸው ታዜር እናታቸው ሶፍያ/አህየዋ/ በቅድስና የሚኖሩ እግዚአብሔርን በቅድስና በንጽህና የሚያገለግሉ ነገር ግን ልጅ ያላገኙ መካኖች ነበሩ። ስለሆነም ጌታ ሆይ ደስ የሚያሰኝህ በትዕዛዝህም የሚኖር ልጅ ስጠን እያሉ እግዚአብሔርን ይለምኑ ነበር፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ስለ እግዚአብሔር ቸርነት ሲነጋገሩ ንግስት ሶፍያ የሐና እመ ሳሙኤልን ጸሎት በመጥቀስ እሷም እንደ ሐና ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን እንድትለምን ንጉሱን ጠየቀችው፡ ንጉሱም “ ኦ ብእሲቶ ሰናየ ኁለይኪ” አንቺ ሆይ መልካም አስበሻል በማለት በምክሯ ተስማምቶ ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን በጸሎት እንድትጠይቅ ፈቀደላት፡፡ ንግስት ሶፍያም የካቲት 18 ቀን ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን መለመን ጀመረች፡፡ ከጸሎቷም ጥቂቱ “ በኪሩቤል ላይ የምትኖር፣ የቀለያትንም (ጥልቅ ባህርንም) የምትመለከት ጌታዬ ፈጠሪዬ ሆይ አቤቱ ጸሎቴንና ልመንያን ስማኝ፣ ልቅሶየንም አድምጥ ቸላ አትበለኝ” የሚል ነበር፡፡

Read more

ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ

አባቷ  ባሕር አሰግድ እናቷ  ደግሞ  ክርስቶስ አዕበያ  ይባላሉ። ትውልዷ ከዳሮ /ምስራቅ ኢትዮጵያ/ ወገን ነው። ወንድሞቿ ዮሐንስና ዘድንግል በንጉሥ  ሱስንዮስ ጊዜ ታላላቅ ባለስልጣናት ነበሩ። እናት አባቷ  በህግ በስርዓት ካሳደጓት በኋላ ሥዕለ ክርስቶስ የሚባል የስስኑዮስ የጦር አበጋዝ ቢትወደድ  አግብታ 3 ልጆች መውለድዋን ገድሏ ይናገራል። ይህ ቢትወደድ ይኖርበት የነበረው ግንብ ቤት ፍራሽ እስከ አሁን ድረስ በጋይንት ስማዳ ይታያል።

Read more

ኢትዮጵያዊዉ ጃንደረባ

በዓለም የክርስትና ታሪክ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቀዳሚውን ስፍራ የያዘችና ሐዋርያዊት ለመሆንዋ ምስክር ከሚሆኑ ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል ባኮስ ቀዳማዊ ነው። ኢትዮጵያውያን ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ ሕዝበ እግዚአብሔር ከሚባሉ እስራኤል ጋር በአምልኮተ እግዚአብሔር የሚኖሩ ሕዝብ ስለመሆናቸው ቅዱስ መጽሐፍ ይመሰክራል። አያሌ የታሪክ መዛግብትና የአርኪዮሎጂ ምርምር ውጤቶችም ይህንን እውነት ያረጋግጣሉ። እኛም በዚህ የቅዱሳን ታሪክ ዓምድ፣ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ”በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም” ማቴ፭፥፲፬ እንዳለ፤ በረከቱና አርአያነቱ ለትውልድ ይተርፋል በማለት የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ታሪክ ይዘን ቀርበናል። የቅዱሳን አማላጅነትና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
Read more