“ዘይሁብ መርሐ ርቱዐ ለቤተ ክርስቲያን – ለቤተ ክርስቲያን ቅን መሪ የሚሰጥ”

(ጸሎተ ኪዳን – ዘሠርክ)
በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

ቤተ ክርስቲያን የምንላት ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስ ከፍጹምና ከማይነገር ፍቅሩ የተነሣ ሰው እስከ መሆን፣ ሰው ሆኖም በዚህ ዓለም ከኃጢአት በስተቀር እንደ ሰው መኖርን፣ ከዚያም በቀራንዮ ቅዱስ ሥጋውን እስኪቆርስላትና ክቡር ደሙን እስኪያፈስላት ድረስ የደረሰላትና የመሠረታት የምእመናን አንድነት (ጉባኤ) ናት። “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላእለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” የምንለው ለዚህ ነው። ቤተ ክርስቲያን በወንጌል መሠረትነት በኢየሱስ ክርስቶስ ራስነት በምእመናን አካልነት የተመሠረተች ጉባኤ ናት።

ተጨማሪ ያንብቡ

ደብረ ታቦር

በዲን. ኃይሌ ታከለ

ነሐሴ 12፣ 2004 ዓ.ም.

Debre_Tabor

ደብረ ታቦር ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ታቦር በተሰኘው ረጅም ተራራ የገለጠበት ታላቅ በዓል ነው።  በማቴ 16፥13-19 እንደምንመለከተው ኢየሱስ በፊልጶስ ግዛት ከምትሆን ከቂሣርያ አውራጃ በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን:- ”ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል?” ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፣ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት። እርሱም ደግሞ እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንኩ ትላላችሁ አላቸው። ከደቀ መዛሙርቱም መካከል ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ በማለት መለሰለት። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፡- ”የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ። እኔም እልሃለሁ አንተ ጴጥሮስ ነህ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም። የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል” በማለት ተናገረው።

Read more

ጾመ ፍልሰታ

በኤርምያስ ልዑለቃል

ሐምሌ 30፣ 2004 ዓ.ም.

filseta

“አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ” ሉቃ 1 ፡28

ጾመ ፍልሰታ በከበረች ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት የምንኖር የእግዚአብሔር ልጆች በረከትን ከምንቀበልባቸው የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ሲሆን በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 16 ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ፍቅር ከወትሮው በበለጠ ሁኔታ ለእግዚአብሔር በመገዛት በተሰበረ ልቦና እና በተሰበሰበ ህሊና ከጥሉላት መባልዕት (ለሰውነት ብርታት ከሚሰጡ የእንስሳት ተዋፅኦ እና ቅባትነት ካላቸው ምግቦች) እና ከክፉ ስራ ሁሉ ተለይተን በበረከት የምንትረፈረፍበት የጾም ወቅት ነው። ፍልሰታ የሚለው ቃል ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መዛወር፣ የነበሩበትን ስፍራ ለቆ ወደ ሌላ ስፍራ መወሰድ ወይም መፍለስ ማለት ነው።

Read more

የቅድስት ማርያም ዘር ነኝ

በዲን. ብርሃኑ ታደሰ

ግንቦት 1፣ 2004 ዓ.ም.

አባታችን አብርሃም እውነተኛውን አምላክ ለሚያመልኩ ሁሉ ታላቅ የእምነት አባት ነው። በእርግጥም አምላኩን ፍጥረትን በመመርመር ማግኘቱ፣ አምላኩን ብሎ ቤተሰቡን ተለይቶ መውጣቱ፣ ልጁን ለመሰዋት ፍጹም ፈቃዱን ማሳየቱ ሁሉ ለእምነት አባትነቱ ማሳያዎች ናቸው። ከሁሉ የሚልቀው ከእርሱ አስቀድሞ ከሙታን መካከል የተነሱ ሳይኖሩ፣ ዘርህ በይስሐቅ ይጠራልሃል ከተባለ በኋላ ልጅህን ሰዋልኝ ሲባል፣ እነዚህን ሁለት የሚጣሉ የሚመስሉ ሐሳቦችን በእምነቱ አስታርቆ ማለት ቢሞት እንኳን ያስነሳዋል ብሎ አምኖ ልጁን ሊሰዋ ወደ ተራራ መውጣቱ ነው።(ዕብ11፥19) የሰው ሕሊና ጊዜ ሲያገኝ አንድን ነገር ደጋግሞ ማሰቡ አይቀርም፤ አብርሃም ግን የሦስት ቀን መንገድ ሲሄድ ይህ እምነቱ ንውጽውጽታ አልነበረውም – እፁብ ነው።Lideta_Le_Mariam_1

እኛ ክርስቲያኖች – የእግዚአብሔር ወልድን ሰው መሆን፣ ለኛ ብሎ መከራ መቀበል፣ በኋላም የቤዛነቱን ሥራ ሲፈጽም በአባቱ ክብር መቀመጡን ስለምናምንና ስለተጠመቅን የእግዚአብሔር ልጆች ሆነናል። ይህ ልጅነት በፊት እንደነበረው ከሥጋ የመጣ አይደለም፤ መጽሐፍ – “ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፤ ከመንፈስ የተወለደ ግን መንፈስ ነው።” እንዲል፤ ልጅነታችን በጸጋ ከመንፈስ ቅዱስ የተነሳ ነው። (ዮሐ3) ቅዱስ ጴጥሮስ ደግሞ ይህንን ሲያጸናው የተወለድነው ከሚጠፋ ዘር አይደለም ይለናል። (1ጴጥ1፥22)

Read more

የጾም ጥቅም

ጾም ማለት ለተወሰኑ ሰዓታት ከእህል እና ከውሃ (ጥሉላት መባልዕትን ጾሙ እስኪፈጸም ፈጽሞ መተው) እንዲሁም ለተወሰኑ ጊዜያት ከሥጋ ፈቃዳት መከልከል ነው።። ስለዚህ መጾም ማለት በጾም ወቅት የምግብ ዓይነትን መለወጥ ብቻ ሳይሆን የምንወደውን የሥጋ ፍላጎት ስለ እግዚአብሔር ብለን መተው ነው።። የሥጋ ፍላጎት የዓለምን ምኞት መፈጸም ሲሆን ይህን ነገር የምንገታው ደግሞ ራሳችንን በጾም በመግዛት ነው። ”ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ- ነፍሴን በጾም አስመረርኋት” መዝ. 68፥10 እንዲል። ታሪካቸው በትንቢተ ዳንኤል ተጽፎ የምናገኘው ሦስቱ ወጣቶች በንጉሥ ቤት እየኖሩ የተሻለ ነገር መመገብ ሲችሉ እግዚአብሔርን ስለ መውደድ ብለው በንጉሡ ቤት ከሚዘጋጀው ማለፊያ ምግብ ይልቅ ጥራጥሬን መመገብ መረጡ። ትን ዳን. 1፥8-16። በተጨማሪም እንደ ዮሴፍ እግዚአብሔርን በመፍራት ምክንያተኝነትን በመተው ከኃጢአት መጾም ነው:፡ ዮሴፍ ኃጢአቱን ለመሥራት የእመቤቱን ፈቃደኝነትና የእርሱን ወጣትነት እንደ ምክንያት አላቀረበም። ነገር ግን ፈጣሪውን ዘወትር በፊቱ በማድረጉ ከኃጢአት ለመጾም ችሏል። ዘፍ 39፥7-13;: ስለዚህ ጾም ማለት እያለንና ማድረግ እየቻልን ስለ እግዚአብሔር ብለን መተው ነው።

Read more

ደብረ ዘይት

ደብረ ዘይት ማለት የወይራ ዛፍ ያለበት ተራራ ማለት ነው፡፡ቦታው ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ የሚገኝ የወይራ ዛፍ የበዛበት ተራራ ሲሆን ስሙም ከወይራ ዛፉ:-ደብረ ዘይት (የወይራ ዛፍ ተራራ) በመሰኘት ተገኝቷል። በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ደብረ ዘይት በዓል ሆኖ የሚከበርበት ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረዘይት ተራራ ላይ ሳለ ለቅዱሳን ደቀመዛሙርቱ ስለ ዓለም ፍጻሜ እና ስለ ዳግም ምጽአቱ ስላስተማራቸዉ በጌታችን ትምህርት መሰረት ነገረ ምጽአቱን (የመምጣቱን ነገር) እንድናስታዉስ ወይም እያሰብን እንድንዘጋጅ ለማድረግ ነዉ።debre Zeyt

Read more

የጥምቀት አስፈላጊነት

በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከኒቂያ ጉባኤ በኋላ ከተነሱት አባቶች አንዱ “በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም” ራእይ ፳፥፮ የሚለውን የወንጌላዊው ዮሐንስን አባባል በተረጎመበት የእግዚአብሔር ከተማ በሚለው መጽሐፉ ላይ ፊተኛው ትንሣኤ የተባለው ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና የምናገኝበት ጥምቀት እንደሆነ ገልጿል (De Civitate Dei,xx,6)።

Read more

“ተወልደ ኢየሱስ በቤተ ልሔም ዘይሁዳ”(ቅ. ያሬድ)

ታኅሣሥ 28 ቀን 2004 ዓ.ም. 

በቀሲስ ደመቀ አሸናፊ


በጌታችንና በአምላካችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተደረገልን ፍፁም ሥርየትና እርቅ ግልጥ ሆኖ የተጀመረው በነገረ ልደት ነው። የጌታችን ልደት በነገረ ድኅነት ትልቅ ስፍራ የያዘና እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ፍፁም ልዩ መሆኑን ያሳየ ነው። መስተፃርራን የነበሩ ሰማይና ምድር፣ ሰውና መላእክት በአንድነት ለምስጋና ታድመዋል። የእረኞች አንደበት ከመላእክት ጋር ለሰማያዊ ምስጋና ብቁ የሆነበት፤ ግዕዛን የሌላቸው እንስሳት ሰራኢ መጋቢያችን፣ በዘባነ ኪሩቤል በሰማያት የምትገለጥ አንተ ነህ ሲሉ እስትንፋሳቸውን የገበሩለት፤ የምድር ነገስታት በሥልጣንህ ሽረት በመንግሥህ ህልፈት የሌለብህ የነገስታት ንጉሥ አንተ ነህ ሲሉ ወርቅን ለመንግሥቱ፣ ዕጣንን ለክህነቱ፣ ከርቤን ለህማሙ ዕጅ መንሻን ያበረከቱለት፤ ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ከጻድቁ ዮሴፍ ጋር ያን ልዩ ክብር የዩበት፤ ይህ ልደት በእውነት ልዩ ነው።

Read more

የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን

መግቢያ

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በተለያየ ጊዜ ካህናት እና ምእመናን የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት በተባለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዴት ሊኖሩ እንደሚገባ ድርሻቸውም ምን እንደሆነ ያስተምራቸው ነበር:: ለምሳሌ የመንፈስ ልጁ የሆነ ቅዱስ ጢሞቴዎስን በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት ሲኖር ምን ማድረግ እንዳለበት እንዲህ በማለት መክሮታል:-“በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዐምድና መሠረት የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው::” (1ጢሞ 3፥15)

Read more

ሕይወት በባዕድ ምድር (፪ጴጥ. ፪፥፰)

የርዕሳችን መነሻ የሆነው በ፪ኛ ጴጥሮስ ምዕራፍ ፪ ላይ የምናገኘው ታሪክ ነው። “ጻድቅ ሎጥም እያየና እየሰማ፣ አብሮአቸውም እየኖረ በክፉ ሥራቸው ዕለት ዕለት ጻድቅት ነፍሱን ያስጨንቃት ነበር።” ፪ጴጥ. ፪፥፰

ሎጥ ኃጢአትን የዕለት ከዕለት ተግባራቸው ካደረጉ ሰዎች ጋር ለመኖር የተገደደው በዘፍ ፲፫ ላይ እንደምናነበው ከአጎቱ ከአብርሃም ጋር ይኖርበት የነበረው ቦታ ስለጠበባቸው በእረኞቻቸው መካከልም እየተፈጠረ የነበረው ጥላቻ ወደ እነርሱ እንዳይጋባ ራቅ ወዳለ ቦታ መሄድ ስለነበረበት ነበር። ለመለያየት ሲወስኑም ለሎጥ እንዲመርጥ ዕድል በተሰጠው ጊዜ የመረጣት ውሃ የሞላባትን ለምለሟን ሰዶምን ነበር። ሎጥ ግን በጎረቤቶቹ መካከል እየኖረ ዕለት ዕለት የሚሠሩትን ሥራ እያየና እየሰማ

Read more