የግቢ ጉባኤ አንደኛ አመት ተማሪዎች ምዝገባ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማ/መ/ ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል በዩኬ፣ በጀርመን እና በሌሎች የአዉሮፓ ሀገሮች በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና ኮሌጆች የሚማሩ የቤተ ክርስቲያን ልጆችን የኢንተርኔት መገናኛዎችን በመጠቀም መሰረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በማስተማር ላይ የሚገኝ ሲሆን የመጪዉን የ2013 ዓ/ም ትምህርት ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቆ አዳዲስ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን በመመዝገብ ላይ ይገኛል። በመሆኑም በዚህ የቨርቹዋል ግቢ ጉባኤ በመታቀፍ ለመማር የምትፈልጉ ኦርቶዶክሳውያን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንድትሆኑ እየጋበዝን ከዚህ በታች ያለዉን የጉጉል ፎርም ሊንክ በመክፈት እንድትመዘገቡ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdg2mI6K3033TDMnpqMMU0HqAVFywD4JrUC1W9rtnWdJX_UiQ/viewform