ሐዊረ ሕይወት (የሕይወት ጉዞ) በሀገረ ጀርመን

ታህሣስ 26 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ.ሰ.ማ.መ.ማኅበረ ቅዱሳን የጀርመን ቀጠና ማዕከል ሁለተኛውን የሐዊረ ሕይዎት ጉዞ ከመጋቢት 11 – 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ ጀርመን ሀገር የሚገኘው ግብጽ ቅዱስ እንጦንስ ገዳም እንደሚያካሂድ አስታወቀ። በዚህ መርሐ ግብር ላይ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ወንጌል እንዲሁም ከምዕመናን ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ ይሰጥበታል። በጉዞው ላይ ከተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት የሚመጡ ምዕመና እንደሚሳተፉ ይጠበቃል። ቀጠና ማዕከሉ ለህዝበ ክርስቲያኑ በጉዞው ላይ በመሳተፍ ቃለ እግዚአብሔርን እንዲመገቡና በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወንድሞች እና እህቶች የሚደረገውን የምክርና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት እንዲደግፉ ጥሪውን አስተላልፏል።

2ndHawire HiwotInGermany1