የሆላንድ ንዑስ ማዕከል ዓውደ ርዕይ አካሄደ

ሚያዚያ 07 ቀን 2011 ዓ.ም

በሆላንድ ንዑስ ማዕከል

በሆላንድ አምስፎርት ከተማ “ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን አስተምሮዋን እንጠንቅቅ፣ ድርሻችንን እንወቅ” በሚል ርዕስ ዓውደ ርዕይ ተካሄደ፡፡በሐመረ ኖህ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ውስጥ ቅዳሜ ፳፩ / ፪ሺ፲፩ ዓም የተደረገው ይህ ዐውደ ርእይ ቀድሞ ከተካሄደው አውደ ርእይ ከረጅም ጊዜ በኋላ ቆይቶ የተካሄደ መሆኑን የቆዩ የንዑስ ማዕከሉ አባላት ይናገራሉ። በአራት ክፍል የተዘጋጀው ይህ ዓውደ ርዕይ በምስል ወድምጽ በተደገፈ ገለጻ ቀርቧል።ቤተክርስቲያን ማናት እና አስተምሮዋ በክፍል አንድ ሲቀርብ፤ ሐዋርያዊው ተልእኮ እንዲሁም በተልእኮው  የገጠሙ ተግዳሮቶችና የተደረጉ ተጋድሎዎች በክፍል ሁለትና ሶስት በቅደም ተከተል ቀርበው፤ በመጨረሻም በክፍል አራት የምዕመናን ድርሻ ምን ሊሆን እንደሚችልም ያመላከተም ነበር።

Image may contain: one or more people, people standing and wedding Image may contain: 1 person, indoor

በአውደ ርእዩ የተሳተፉ ምዕመናንም እንዲህ አይነት ዝግጅት በየዓመቱ ቢደረግ፤ እኛ ያየነውን በሌሎች አጥቢያዎች ያሉ ምዕመናንም እንዲያዩት ቢደረግ በሕብረት ወደ መስራት ያመጣን ይሆናል በማለት አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ በተለይ ትዕይንት ክፍል ሶስትና አራት የቀደሙ አባቶቻችንና እናቶቻችን ይህችን ቤተክርስቲያን እንዴት እንዳቆዩልንና ዛሬስ ምን እያደረግን እንደሆነ የሚያነጻጽር በመሆኑ፤  ወደ ራሳችን ተመልሰን እራሳችንን እንድመለከት አድርጎናል ብለዋል።

ትዕይንቱን መርቀው የከፈቱት የደብሩ አስተዳዳሪ አባ ኃይለማርያምም ማኅበሩ ለቤተክርስቲያን ፈርጥ መሆኑን እናውቃለን ግን በሆላንድ ያለው እንቅስቃሴ እኔ በማውቀው ውስን ነው፡አሁን ያየነው መርሐ ግብር በራሱ ትልቅ ለውጥ መሆኑን መመልከት ችያለሁ። ከዚህ ቦኃላም ማኅበሩ ከቤተክርስቲያን የተረከበውን የልጅነት አደራ እንደሚወጣ እገምታለው  ብለዋል፡፡ አያይዘውም ተጀምሮ እስኪያልቅ ምዕመኑ ሳይሰለች እንዲቆይ ያደረገበት የጊዜ አጠቃቀምና አቀራረብ ዘዴ የማኅበሩን ማንነት ያሳየበት ነው ብለው ከ አውደ ርዕዩ ቦኃላ አስተያየታቸውን ገልፀዋል፡፡ የሰበካ ጉባኤው አባላትም በመርሐግብሩ ተደስተው ሌሎች መርሐ ግብራትንም ማኅበሩ በአጥብያቸው እንደሚያደርግ እና ለዚህም የሰበካ ጉባዔው እና ምእመናንም በማንኛዉም ነገር ለመተባበር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።

Image may contain: one or more people and indoor

የሆላንድ ንዑስ ማዕከል በአውሮጳ ማዕከል ስር ካሉት ንዑስ ማዕከላት አንዱ መሆኑም ይታወቃል፡፡

ወስብሃት ለእግዚአብሔር