«ሕፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉአቸው አትከልክሉአቸውም፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና።» ሉቃ 18:16

ሠለስቱ ደቂቅ

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች?ደህና ናችሁ ልጆች? ዛሬ ስለ ሦስቱ ልጆች ታሪክ እንነግራችኋለን በደንብ ተከታተሉን እሺ፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፣ በድሮ ጊዜ እግዚአብሔርን የማይፈራ ናቡከደነፆር የሚባል የባቢሎን ንጉሥ ነበር፡፡ይህም ንጉሥ ከወርቅ የተሰራ ትልቅ ጣኦት አቁሞ ሕዝቡንም ሁሉ ሰበሰበና ለጣኦቱ እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ ለጣኦት ያልሰገደ ግን በእሳት ውስጥ ይጣላል ብሎ አዋጅ አስነገረ፡፡

Read more

የጌታችን ትንሣኤ

ልጆች ስለ ጌታ ከሞት መነሣት ሰምታችሁ ታውቃላችሁ? እስቲ ትንሽ ስለ ትንሣኤው ልንገራችሁ:: ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ዓርብ ቀን በሐሰት ሰቅለው ከገደሉት በኋላ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ሥጋውን ከመስቀል ላይ አውርደው በንጹህ በፍታ ገንዘው በአትክልት ቦታ በሚገኝ አዲስ መቃብር ውስጥ ቀበሩት። ትልቅ ድንጋይም አንከባለው የመቃብሩን አፍ ዘጉት። በአይሁድ የታዘዙ ብዙ ጭፍሮች (ወታደሮች) የጌታችንን መቃብር ይጠብቁ ነበር።

ልጆች፣ ጌታችን ከሞት ሲነሣ የታዩትን ድንቃ ድንቅ ነገሮች ታውቃላችሁ? Read more