• እንኳን በደኅና መጡ !

የመስቀል (ደመራ) በዓል በፊንላንድ ርዕሰ መዲና በሄልሲንኪ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ በድምቀት ተከበረ።

በአውሮፓ ማእከል ኅ/ኤ/ሚ ክፍል መስከረም 26 ቀን 2009 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅነት በተካሄደው የደመራ በዓል ላይ የደብሩ አገልጋይ ካህናት ዲያቆናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን እና ምዕመናን ተገኝተዋል።  በተጨማሪም የሄልሲንኪ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን፣ […]

‹‹መስቀል ለእለ ነአምን መድኅን›› ቅዱስ ያሬድ

በመጋቢ ሀዲስ ምስጢረ ስላሴ ማናዬ መስከረም 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ‹‹መስቀል ለእለ ነአምን መድኅን – መስቀል ለምናምን መድኃኒት ነው››። ስለነገረ መስቀሉ ከተናገሩ ሊቃውንት የኢትዮጵያው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ትልቅ ድርሻ አለው። በአምስቱም ድርሰቶቹ በሰፊው ስለ መስቀል ዘምሯል፣ ተናግሯል፣ አመስጥሯል። ከላይ ያነሳነውን ኃይለ ቃል የተናገረውም እርሱ ነው። ምክንያቱም የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ስለ ነገረ ድኅነነት ያጠነጥናሉ። እግዚአብሔር በነገረ […]

የደብረ መዊ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ

በአውሮፓ ማእከል ኅ/ኤ/ሚ ክፍል መስከረም 9 ቀን 2009 ዓ.ም በስዊድን ሉንድ ከተማ የደብረ መዊ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያ በብፁዕ አቡነ ሙሴ የደ/ም/ም እና የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ነሐሴ 29 ቀን 2008 ዓ.ም. ታቦተ ህጉ ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል።

«መኑ ውእቱ ብእሲ ዘይፈቅድ ሐይወ ወያፈቅር ይርአይ መዋዕለ  ሠናያተ »

በመምህር ፍቃዱ ሣህሌ ጳጕሜ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ሕይወትን የሚፈቅድ ሰው ማን ነው ? በጎ ዘመንንም ለማየት የሚወድድ ማን ነው ? መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊት እንደ ሰውነቱ በርካታ ጥያቄዎችን ጠይቋል። እንደ መንፈስ ቅዱስ ማደሪያነቱ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ለጥያቄዎችም መልስ ሰጥቷል። ከላይ የተቀምጠው ጥያቃዊ  ኃይለ ቃልም በተመሳሳይ ሁኔታ ያቀረበው ጥያቄ ሲሆን ለሁላችንም ጥቅም  ይሆን ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እርሱ […]

በጀርመን በርሊን ዐውደ ርእይ እና ስብከተ ወንጌል መርሐግብር ተካሄደ

በጀርመን ንኡስ ማእከል ጳጕሜ 3 ቀን 2008 ዓ.ም. በጀርመን ርእሰ ከተማ በበርሊን ነሐሴ ፯ እና ፰፣ ፳፻፰ ዓ.ም “ለሁለንተናዊ የቤተክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል መሪ ቃል የዐውደ ርእይ እና የስብከተ ወንጌል መርሐግብር ተካሄደ። ይህንን በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ከበርሊን ደብረ ገነት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባበር ያዘጋጁትን መርሐግብር የከፈቱት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ቆሞስ […]


ይህን በመጫን ይለግሱ

የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ይደግፉ!



የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ  


ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች 


የቴሌቪዥን እና ራዲዮ አገልግሎት 

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

©2019. Mahibere Kidusan Europe Center - All Rights Reserved. Website by MK-IT