ማኅበረ ቅዱሳን የሥራ አመራር ጉባኤ ምርጫ አካሄደ

በእንዳለ ደምስስ

ጳጉሜን 2 ቀን 2004 ዓ.ም.

ከነሐሴ 30 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ እየተካሄደ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን 10ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በመጠናቀቅ ላይ ነው፡፡

mk_10th_general_assembly

ጳጉሜን 1 ቀን 2004 ዓ.ም. ጠዋት በተካሄደው የጠቅላላ ጉባኤው ስብሰባ “በማኅበረ ቅዱሳን የአገልግሎት ጉዞ የአባላት ተሳትፎና የወደፊት ሁኔታ” በተመለከተ ጥናት የቀረበ ሲሆን በአባላት ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዷል፡፡ ከሰዓት በኋላ በቀጠለው ስብሰባም “ስልታዊ ለውጥ ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት ከማኅበረ ቅዱሳን ተልእኮና አቅም አንጻር” በሚል በዲ/ን ያረጋል አበጋዝና ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ በአባላት ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በመጨረሻም የጽ/ቤት ግንባታ ሪፓርት ቀርቦ የመርሐ ግብሩ ፍጸሜ ሆኗል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

ቅዱስ ሲኖዶስ ጸሎተ ምህላ እንዲደረግ ወሰነ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ነሐሴ 30/2004 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኅን በሰጠው መግለጫ ከጳጉሜ 1 ቀን 2004 ዓ.ም. እስከ መስከረም 10/2005 ዓ.ም. ድረስ ምእመናን ለሁለት ሱባኤያት በመላዋ ኢትዮጵያና በውጭ ሀገር በሚገኙ አህጉረ ስብከቶች በሚገኙ ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምህላ እንዲደረግ ወስኗል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ጸሎተ ምኅላውን ያወጀበት ምክንያት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በነበሩበት ዘመን በሃይማኖታዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሥራ የሠሩ አባት እንደነበሩ ጠቅሶ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ፤ ለሀገሪቱ ሰላምና አንድነት የሚበጅ ተተኪ አባት(ፓትርያርክ) እግዚአብሔር ባወቀ መርጦ እንዲያስቀምጥ ካህናትና ምእመናን በጸሎተ ምኅላው እንዲሳተፉ አሳስቧል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ነሐሴ 30/2004 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኅን በሰጠው መግለጫ ከጳጉሜ 1 ቀን 2004 ዓ.ም. እስከ መስከረም 10/2005 ዓ.ም. ድረስ ምእመናን ለሁለት ሱባኤያት በመላዋ ኢትዮጵያና በውጭ ሀገር በሚገኙ አህጉረ ስብከቶች በሚገኙ ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምህላ እንዲደረግ ወስኗል። ቅዱስ ሲኖዶስ ጸሎተ ምኅላውን ያወጀበት ምክንያት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በነበሩበት ዘመን በሃይማኖታዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሥራ የሠሩ አባት እንደነበሩ ጠቅሶ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ፤ ለሀገሪቱ ሰላምና አንድነት የሚበጅ ተተኪ አባት(ፓትርያርክ) እግዚአብሔር ባወቀ መርጦ እንዲያስቀምጥ ካህናትና ምእመናን በጸሎተ ምኅላው እንዲሳተፉ አሳስቧል።

ምንጭ፡- ማኅበረ ቅዱሳን – ዋናው ማዕከል ድረ ገጽ

ወቅታዊ ዜናዎች


ሌሎች ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ዜናዎችን ለማንበብ “ዜና” በሚለው አምዳችን ሥር ከዋናው ማእከል የሚለውን “ሜኑ” በመምረጥ በዋናው ማእከል ድረ ገጽ ላይ የወጡ ጽሁፎችን በቀጥታ ማንበብ ይችላሉ።

 

ስለ ቅዱስ ፖትርያርኩ ሥርዓተ ቀብር መግለጫ ተሰጠ

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፖትርያርክ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት፣ የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዚዳንት ሥርዓተ ቀብር በማስመልከት ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጠ፡፡

Read more

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አረፉ

አምስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳሳ ዘአክሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ፕሬዚዳንት ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም. ከንጋቱ 11:00 ሰአት ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል።

abune_paulose

እግዚአብሔር አምላክ የቅዱስነታቸውን ነፍስ በደጋግ አባቶች አቅፍ ውስጥ ያኑርልን፣ አሜን

አውሮፓ ማዕከል ፲፫ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሔደ

ሐምሌ ፲፩ ቀን  ፳፻፭ .ም.

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ማኀበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማዕከል ፲፫ኛ ጠቅላላጉባኤውን ከሐምሌ ፭ እስከ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ አካሔደ። በጉባኤው ከተለያዩ የአውሮፓ አገራት የመጡ የማኀበሩ አባላት፣ ካህናትና የማኅበሩን አግልግሎት በተለያየ መንገድ የሚደግፉ ምእመናንተሳተፉ ሲሆን ከዋናዉ ማዕከል ደግሞ ሁለት ልዑካን ተገኝተዋል። 

Read more

ሀገረ ስብከቱ አብይ ጉባዔ አደረገ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በደቡብ፤ ደቡብ ምሥራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በሮም ኢጣሊያ የሀገረ ስብከቱ አብይ ጉባዔ ተደረገ።

Read more