በጀርመን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተመሰረተ።

በጀርመን ን/ማእከል 

ጥር  13 ቀን 2010 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በም/ም/ደ/አውሮፓ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤ/ማ/መምሪያ አስተባባሪነት በጀርመን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተመሰረተ።

በሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤ/ማ/መምሪያ ኃላፊ መልአከ ኃይል አባ ዘድንግል አስተባባሪነት ከሰ/ት/ቤቶች አመራሮች ጋር በተካሄደው የመነሻ ስብሰባ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለመመስረት የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎችን የሚያከናውን አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ የተመረጠ ሲሆን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መተዳደሪያ ደንቡን ከዚህ በፊት በሰሜን አሜሪካ የተሠራውን መሠረት በማድረግና ህገ ቤተክርስቲያንን በጠበቀ መልኩ አርቅቆ የማቅረብና የማጸደቅ፥ የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ተወካዮች ሰብስቦ የማወያየት እና የሰንበት ትምህርት ቤቶችን አባላትን ስለ አንድነቱ ዓላማ እንዲረዱ የማድረግ ተግባራትን በኃላፊነት እንዲመራ ለኮሚቴውም ተስጥቶት ነበር። Read more

በአውሮፓ የሕፃናት እና ታዳጊዎች ሥርዓተ ትምህርት ተመረቀ

በእንግሊዝ ንዑስ ማእከል

ኅዳር 13 ቀን 2010 ዓ.ም.

በምረቃ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሠራተኞች እና ካህናት በከፊል

በምረቃ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሠራተኞች እና ካህናት በከፊል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤ/ማ/መ/ ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል የተተኪ ትውልድ ሥልጠና ክፍል አስተባባሪነት የተዘጋጀ ከኢትዮጵያ ውጪ የሚኖሩ ሕፃናት እና ታዳጊዎችን ለማስተማር የሚያግዝ ሥርዓተ ትምህርት በእንግሊዝ አገር በለንደን ከተማ በደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም ተመረቀ፡፡ Read more

በጀርመን ኑረንበርግ ዐውደ ርእይ እና የስብከተ ወንጌል መርሐግብር ተካሄደ

በጀርመን ማእከል

ጥቅምት 20 ቀን 2010 ዓ.ም.

በደቡባዊቷ የጀርመን ከተማ ኑረንበርግ ጥቅምት 11 እና 12 2010 ዓ.ም “አብረን እንሥራ ለውጥ እናመጣለን” በሚል መሪ ቃል የዐውደ ርእይ እና የስብከተ ወንጌል መርሐግብር ተካሄደ። ይህንን በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል  የጀርመን ንዑስ ማእከል ከኑረንበርግ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ፍኖተ ቤተከርስቲያን ገዳማት እና የአብነት ትምህርት ቤቶች እና  ማኅበረ ቅዱሳን የሚሉ ሦስት ትዕይንቶች የተከፋፈለውን ዐውደ ርእይ  ከ150 በላይ ምእመናን ጎብኝተውታል። በተለይም የዐውደ ርእዩ ዋና ጉዳይ በሆነው የኢትዮጵያ ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ለእምነትና ለታሪክ መጠበቅ እና  ለዕውቀት፣ ትውፊትና ባሕል ከትውልድ ወደ ትውልድ መሸጋገር ያበረከቱትና እያበረከቱት ያለው አስተዋኦ  እንዲሁም አሁን ያሉበት ወቅታዊ ችግሮቻቸው ላይ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል። በተጨማሪም ችግሮቹን ለመፍታት በመላው ዓለም በተለይም በአውሮፓ ያሉ ምእመናን በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት አስተዋፅዖ እያደረጉባቸው ያሉትን  በርካታ ጊዜያዊ እና ዘላቂ መፍትሔዎች በቪዲዮ በታገዘ ማብራሪያ ለተመልካች ቀርበዋል። በሁለቱ ቀናት በነበረው የስብከተ ወንጌል መርሐግብርም በመርጌታ ይቻለዋል ጎሽሜ እና በቀሲስ ዶ/ር ያብባል ሙሉዓለም አገልግሎትን የተመለከቱ ትምህርቶች ሰጥተዋል። Read more

በኮፐንሀገን የደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ዐቢይ የአዲስ ዓመት መንፈሳዊ ጉባኤ አካሄደ።

በዴንማርክ ግንኙነት ጣቢያ

መስከረም 10 ቀን 2010 ዓ.ም.

ባሳለፍነው ቅዳሜ መስከረም 6 እና እሑድ መስከረም 7 ቀን 2010 ዓ.ም. (September 16 and 17 /2017) በዴንማርክ ኮፐንሀገን የደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ደብር የአዲሱን ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ ዐቢይ የርእሰ አውደ ዓመት ጉባኤ አድርጓል። የጉባኤውም መሠረታዊ ዓላማ በሥራ፣ በትምህርት እና በተለያዩ የኑሮ ሁኔታዎች ከአገር ርቀው ያሉ “ዝርዋን ምዕመናንን” ሀገራቸውን ባህላቸውን ይልቁንም ሃይማኖታቸውን በቤተክርስቲያናቸው በኩል እንዲያውቁ ለማስቻል እና በቋሚነት ሊገለገሉ የሚችሉበትን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መፍትሄም ለመፈለግ ጭምር መሆኑ ተገልጿል። Read more

ሀገረ ስብከቱ ፬ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ።

በጀርመን ንዑስ ማእከል

መስከረም 3 ቀን 2010 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ፣ ምዕራብና ደቡብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ፬ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን  ዓርብ ነሐሴ 26 እና ቅዳሜ ነሐሴ 27 ቀን 2009 ዓ/ም የሀገረ ስብከቱ መቀመጫ በሆነችው በጀርመኗ ሮሰልስሀይም ከተማ አካሄደ። በዚህ ዓመታዊ ጉባኤ የሀገረ ስብከቱ ልዩ ልዩ ሓላፊዎች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎችና የሰበካ ጉባኤ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን ጉባኤው በዋናነት በሀገረ ስብከቱ፣ በአጥቢያዎች እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል የሥራ ክንውን፣ የሂሳብ ዘገባ እና የ2010 ዓ/ም የሥራ ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል።   Read more

የስዊዘርላንድ ግንኙነት ጣቢያ አዉደ ርዕይ አካሄደ።

 በስዊዘርላንድ ግንኙነት ጣቢያ

መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም.

ነሐሴ ፳ እና ፳፩ ፳፻፱ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤ/ማ/ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን አዉሮፓ ማእከል የስዊዘርላንድ ግንኙነት ጣቢያ ከስዊዘርላንድ የሎዛን ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር በስዊዘርላንድ ሀገር ለሁለተኛ ጊዜ ልዩ የአብነት እና የገዳማት ቀን በሎዛን ከተማ አካሂዷል። የዕለቱ መሪ ቃል ”ኑ አብረን እንስራ፤ ለውጥም እናመጣለን” የሚል ነበር። መርሐ ግብሩን በስዊዘርላንድ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ኃይለ ጊዮርጊስ መሪነት በጸሎተ ተጀምሯል።  ከጸሎቱ መርሐ ግብር በኃላ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ኃይለ ጊዮርጊስ የእንኳን አደረሳችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም ከኢትዮጵያ የመጡትን ልዑካን አመስግነው ቤተክርስቲያናችን ዛሬ ያለንበት ድረስ ለመድረስ ገዳማት እና የአብነት ትምህርት ቤቶች ያደረጉትን አስተዋፅኦ ገልፀው አውደ ርዕዩን በይፋ ከፍተዋል። Read more

በእንግሊዝ ሀገር የመጀመሪያው ሐዊረ-ሕይወት ተካሄደ

በዩናይትድ ኪንግደም ንዑስ ማእከል

ነሐሴ 8 ቀን 2009 ዓ.ም.

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤ/ማ/ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን አዉሮፓ ማእከል የዩናይትድ ኪንግደም ንዑስ ማእከል ያዘጋጀዉ የመጀመሪያ ዙር የሐዊረ-ሕይወት መርሐ ግብር ሐምሌ 29 ቀን 2009 ዓ.ም. በዩናይትድ ኪንግደም የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ማእከል (ስቲቪኔጅ) ተካሄደ። በተለያዩ የእንግሊዝ ከተሞች የሚኖሩ ከ200 በላይ የሚሆኑ ምእመናን መነሻቸዉን ለንደን እና በርሚንግሃም ከተሞች ባደረጉ አራት አዉቶቡሶች ወደ ቦታዉ ተጉዘዋል። Read more

በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማዕከል 17ኛውን ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ።

በአውሮፓ ማእከል ኅ/ኤ/ሚዲያ ክፍል

ሐምሌ 8 ቀን 2009 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል አስራ ሰባተኛውን ጠቅላላ ጉባኤ “ታገኙ ዘንድ ሩጡ “፩ቆሮ ፱÷፳፬  በሚል መሪ ቃል በጀርመን ክሮፍልባህ የግብፅ ቅዱስ እንጦስ ገዳም የአካባቢው አቢያተ ክርስቲያናት አስተዳዲሪዎች ፣ የሀገረ ስብከቱ ተወካይ፣ የማኅበሩ አባላት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ከዓርብ ሰኔ ፴ እስከ እሁድ ሐምሌ ፪ ቀን አካሄደ። Read more

የጣሊያን ንዑስ ማእከል አውደ ርእይ አካሄደ

በጣሊያን ንዑስ ማእከል

ሰኔ 25 ቀን 2009 ዓ.ም.

ማኅበረ ቅዱሳን የጣሊያን ንዑስ ማእከል ግንቦት ፲፱ እና ፳ ፳፻፱ ዓ/ም ከሮም ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር “ አብረን እንስራ ለውጥም እናመጣለን!” በሚል መሪ ቃል ዐውደ ርእይ አካሄደ። ዐውደ ርእዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሕገ ልቡና በሕገ ኦሪትና በሕገ ወንጌል ያደረገችው ጉዞ፣ የገዳማትና አብነት ትምህርት ቤቶችን ታሪክ እና አሁን ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ ዝክረ ቅዱስ ያሬድ እና ማኅበረ ቅዱሳን በሚሉ አራት ዓቢይ  ክፍሎች የተከፈለ ነበረ። Read more

በኖርዌይ ንዑስ ማእከል የመጀመሪያው ሐዊረ ሕይወት ተካሄደ

በኖርዌይ ንዑስ ማእከል

ሰኔ 20 ቀን 2009 ዓ.ም.

በማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል፣ የኖርዌይ ንዑስ ማእከል ከክርስቲያንሳንድ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር በሀገረ ኖርዌይ የመጀመሪያውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በክርስቲያንሳንድ ከተማ መጋቢት ፳፫ እና ፳፬  ቀን ፳፻፱ ዓ.ም አካሔደ። በሐዊረ ሕይወቱ ላይ ከክርስቲያንሳንድ ከተማ እና በአቅራቢያው ከሚገኙ ሌሎች ከተሞች የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ40 እስከ 50 የሚደርሱ ምእመናን ተሳትፈዋል። Read more