የጀርመን ንዑስ ማእከል አራተኛውን የሐዊረ ሕይወት አካሄደ

በጀርመን ንዑስ ማእከል

ሰኔ 20 ቀን 2009 ዓ.ም.

የጀርመን ንኡስ ማእከል ከመጋቢት ፲፯ እስከ መጋቢት ፲፱ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም አራተኛውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በጀርመን የግብፅ አቡነ እንጦንስ ገዳም አካሄደ፡፡ በዚህ ሐዊረ ሕይወት ከጀርመን እና ከሌሎች አውሮፓ ሀገራት የተውጣጡ ካህናት፣ ዲያቆናት እና ምዕመናን የተሳተፉ ሲሆን በጠቅላላ የተጓዦች ብዛት 250 ነበር።  የጕዞ መነሻውን መጋቢት ፲፯ ከቀኑ 11 ሰዓት ከፍራንክፈርት ዋናው ባቡር ጣቢያ በማድረግ ወደ ገዳሙ የአንድ ሰዓት ተኩል ጉዞ በባቡርና ከዛም የቻለ በእግር  የ30 ደቂቃ መንገድ በመጓዝ ወደ ገዳሙ ተደርሷል። በተዘጋጀው መርሐ ግብር መሠረት ዓርብ ምሽት በመጋቤ ሐዲስ ቀሲስ አባተ “የሕይወት ጉዞ” በሚል ርዕስ ትምህርት ለመእመናን ተሰጥቷል። በመቀጠልም ቅዳሜ ጠዋት 11፡30 ኪዳንና ቅዳሴ እንደሚኖር ማሳሰቢያ ከተሰጠ በኋላ የዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት ተዘግቷል። Read more

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን መዝሙራት ከየት ወዴት በሚል ለሦስተኛ ጊዜ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር በእንግሊዝ ለንደን ከተማ ተካሄደ።

በእንግሊዝ ንዑስ ማእከል

ሰኔ 16 ቀን 2009 ዓ.ም.

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን ስም የሚወጡ መዝሙራት ቁጥር እየተበራከቱ ቢሄዱም በተለይ በቅርብ ጊዜ የወጡ አንዳንድ መዝሙራት ግን ከያሬዳዊ ዜማ ይልቅ ለዓለማዊ ዘፈን ያደሉ መሆናቸዉን ተከትሎ ማኅበረ ቅዱሳን ባካሄደዉ ጥናት እየታዩ ያሉትን ችግሮችና የመፍትሔ ሐሳቦችን በመረጃ በማስደገፍ አቅርቦ ነበር። የዚህ ጥናት ዉጤት በተለያዩ የሀገር ዉስጥና የዉጭ ሀገራት ጉባኤያት ላይ የቀረቡ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን የዩኬ (እንግሊዝ) ንዑስ ማእከል ከሚመለከታቸዉ የቤተ ክርስቲያን አካላት ጋር በመተባበር በ2008 ዓ.ም በበርሚንግሃም እና በኖቲንግሃም ከተሞች በእያንዳንዳቸዉ የተሳካ መርሐ ግብር ተካሂዶ ነበር። Read more

በሆላንድ ሐዊረ ሕይወት ተካሔደ።

በሆላንድ ንዑስ ማእከል

መጋቢት 26 ቀን 2009 ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል የሆላንድ ንዑስ ማዕከል የመጀመሪያውን ሐዊረ ሕይወት በሆላንድ ሊቨልደ ግዛት በሚገኘው የግብፅ ኮፕት ቅዱስ ቴዎድሮስ ኦርቶዶክስ ገዳም መጋቢት ፱ ፳፻፱ ዓ.ም. አካሔደ።

ሐዊረ ሕይወቱ በአባቶች ጸሎት የተከፈተ ሲሆን በመቀጠልም የመጀመሪያ የሆነው የነገረ ክርስቶስ ትምህርት በመጋቤ ምስጢር ኅሩይ ኤርምያስ ተሰጥቷል። ከሰአት በኋላ ከተሳታፊዎች ለተነሱ መንፈሳዊ ጥያቄዎች በአባቶች በኩል መልስ ተመልሷል።ከዚያም በኋላ በዲ/ን መስፍን ኃይሌ ነገረ ቅዱሳን የሚመለከት ትምህርት ለጉባዔው ቀርቧል ። Read more

በቩርዝቡርግ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ዐውደ ርእይ ተካሔደ።

በጀርመን ንዑስ ማእከል

መጋቢት 26 ቀን 2009 ዓ.ም

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰ/ት/ቤ/ማ/መምርያ ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል የጀርመን ንዑስ ማእከል እና የቩርዝቡርግ ቅዱስ ማርቆስ ሰበካ ጉባዔ በመተባበር ከየካቲት ፳፭ እስከ የካቲት ፳፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም ዐውደ ርእይ እና የስብከተ ወንጌል መርሐ ግብር አካሄዱ። ዐውደ ርእዩ የቩርዝቡርግ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ በሆኑት በቀሲስ ገብረማርያም እና የአውሮፓ ማእከል ሰብሳቢ በሆኑት በቀሲስ ዶ/ር ያብባል ሙሉዓለም የተከፈተ ሲሆን ፍኖተ ቤተ ክርስቲያን፣ ዝክረ ገዳማት ወቤተ ጉባኤ እና ማኅበረ ቅዱሳን የሚሉ ሦስት ክፍሎችን ያካተተ ነበረ። Read more

የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሁለት የወረዳ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤቶችን አዋቀረ።

በአውሮፓ ማእከል ኅ/ኤ/ሚ ክፍል

የካቲት 2 ቀን 2009 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የወረዳ ቤተክህነት ጽሕፈት  ቤቶችን  አዋቀረ። ሀገረ ስብከቱ የመላው አውሮፓ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ሙሴ መቀመጫ በሆነችው በጀርመን ሀገረ በምትገኘው የሮሰልስሃይም ከተማ ጥር 19 እና  20 ቀን 2009 ዓ.ም ጉባኤውን  አካሂዷል። በጉባኤው ላይ የአህጉረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ፣ በሸንገን ስቴት ውስጥ ባሉ የአውሮፓ ሀገራት ያሉ የሀገረ ስብከቱ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች እና ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችንም አሳልፏል። Read more

የመስቀል (ደመራ) በዓል በፊንላንድ ርዕሰ መዲና በሄልሲንኪ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ በድምቀት ተከበረ።

በአውሮፓ ማእከል ኅ/ኤ/ሚ ክፍል

መስከረም 26 ቀን 2009 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅነት በተካሄደው የደመራ በዓል ላይ የደብሩ አገልጋይ ካህናት ዲያቆናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን እና ምዕመናን ተገኝተዋል።  በተጨማሪም የሄልሲንኪ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን፣ ከከተማው የተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች  እና ጋዜጠኞችም  በበዓሉ ላይ ተካፍለዋል። Read more

የደብረ መዊ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ

በአውሮፓ ማእከል ኅ/ኤ/ሚ ክፍል

መስከረም 9 ቀን 2009 ዓ.ም

በስዊድን ሉንድ ከተማ የደብረ መዊ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያ በብፁዕ አቡነ ሙሴ የደ/ም/ም እና የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ነሐሴ 29 ቀን 2008 ዓ.ም. ታቦተ ህጉ ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል።

14205986_1069889456435877_5576623531079840071_o 14232022_1069885853102904_8227531442228237185_o

Read more

በጀርመን በርሊን ዐውደ ርእይ እና ስብከተ ወንጌል መርሐግብር ተካሄደ

በጀርመን ንኡስ ማእከል

ጳጕሜ 3 ቀን 2008 ..

በጀርመን ርእሰ ከተማ በበርሊን ነሐሴ እና ፳፻፰.ም “ለሁለንተናዊ የቤተክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል መሪ ቃል የዐውደ ርእይ እና የስብከተ ወንጌል መርሐግብር ተካሄደ። ይህንን በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ከበርሊን ደብረ ገነት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባበር ያዘጋጁትን መርሐግብር የከፈቱት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ብርሃነ መስቀል ተድላ ሲሆኑ ዐውደ ርእዩን ብዙ ምእመናን ጎብኝተውታል። ዐውደ ርእዩ ፍኖተ ቤተከርስቲያን፣ ገዳማት እና የአብነት ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ማኅበረ ቅዱሳን የሚሉ ሦስት ትዕይንቶችን ያካተተ ነበር። በተለይም የኢትዮጵያ ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ለእምነትና ለታሪክ መጠበቅ እና ለዕውቀት፣ ትውፊትና ባሕል ከትውልድ ወደ ትውልድ መሸጋገር ያበረከቱትና እያበረከቱት ያለው አስተዋኦ እንዲሁም አሁን ያሉበት ወቅታዊ ችግሮቻቸው በሰፊው የተገለጸ ሲሆን ችግሮቹን ለመፍታት ማኅበረ ቅዱሳን እየወሰዳቸው ያሉ በርካታ ጊዜያዊ እና ዘላቂ መፍትሔዎች በቪዲዮ በታገዘ ማብራሪያ ለጎብኚዎች ቀርበዋል። ከዐውደ ርእዩ በተጨማሪም ከማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል የመጡት መምህር ፈቃዱ ሣህሌ ትምሀርት ሰጥተዋል። Read more

“መዝሙሮቻችን ከየት ወዴት” በሚል ርዕስ በመዝሙራት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ተካሄደ

በእንግሊዝ ንዑስ ማዕከል

ነሐሴ 5 ቀን 2008 ..

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማዕከል የዩኬ (እንግሊዝ) ንዑስ ማዕከልመዝሙሮቻችን ከየት ወዴት” በሚል ርእስ ሐምሌ ፳፬ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም የኖቲንግሃምና የአቅራቢያ ከተሞች ካህናትና ምእመናን፣ የሰንበት ት/ቤት መዘምራንና የንዑስ ማእከሉ አባላት በተገኙበት በኖቲንግሃም ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር አካሄደ። Read more

በማኅበረ ቅዱሳን አዉሮፓ ማዕከል የዩኬ(እንግሊዝ) ንዑስ ማዕከል አስተባባሪነት የተዘጋጀዉ ጉባዔ ተጠናቀቀ

በእንግሊዝ ንዑስ ማዕከል

ሐምሌ 29 ቀን 2008 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ// ቤቶች ማ/ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን አዉሮፓ ማዕከል የዩኬ (እንግሊዝ) ንዑስ ማዕከል ከሁለት አጥቢያ አቢያተ ክርስቲያናት ጋር በመተባበር አዘጋጅቶት የነበረዉ የስብከተ ወንጌል ጉባዔ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ጉባዔው ሰኔ ፳፭ እና ፳፮ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በበርሚንግሃም ደ/መድኃኒት ቅዱስ አማኑኤል እንዲሁም ሐምሌ ፪ እና ፫ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በሊድስ ደ/ ስብሐት መድኃኔ ዓለም አቢያተ ክርስቲያናት የተካሄደ ሲሆን በበርሚንግሃም፣ በሊድስ እና በአቅራቢያ ከተሞች የሚኖሩ በራካታ ምዕመናን ተካፍለዋል። Read more