የአውሮፓ ማዕከል ፲፭ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በፍራንክፈርት ፥ ጀርመን አካሄደ

በብዙኀን መገናኛ እና ቴክኖሎጂ አገልግሎት ክፍል

ሐምሌ 02 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማዕከል አስራ አምስተኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በጀርመን ሀገር በፍራንክፈርት ከተማ በምትገኘው በደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከሰኔ ፳፮ እስከ ፰ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. አካሄደ።

GA 15 1

Read more

ጉባኤያቱ እንደቀጠሉ ናቸው።


በብዙኀን መገናኛ እና ቴክኖሎጅ አገልግሎት ክፍል

ሰኔ 23 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰ//ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ካሉ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በመተባበር «ለሁለንተናዊ የቤተክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ» በሚል መሪ ቃል እያካሄደ ያለው ጉባኤ እንደቀጠለ ነው። ከማዕከሉ ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በሰኔ ፮ ቀን ፳፻፯ ዓ.. ለመጀመሪያ ጊዜ በስዊዘርላድ ሀገር በርን ከተማ ከጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ጋር በመተባበር፤ እንዲሁም ከሰኔ ፲፫ – ፲፬ ቀን ፪፲፻፯ ዓ.ም በግሪክ የአቴና ምክሐ ደናግል ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር ጉባኤያትን አካሂዷል።

በጉባኤያቱ ላይ «ፍኖተ ቤተክርስቲያን፣ ገዳማት እና የአብነት ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ማኅበረ ቅዱሳን» በሚሉ ሶስት ትእይንቶች የተከፋፈለ ዐውደ ርዕይ ተካሂዷል። እንዲሁም ከማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል በመጡት ልዑካን ሰፊ ወንጌል ትምህር የተሰጠ ሲሆን ለገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች ድጋፍም የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ተከናውኗል።

በስዊዘርላንድ በተካሄደው ጉባኤ ላይ ከ፹ በላይ ምዕመናን እና ካህናት የተሳትፉበት ሲሆን በግሪክ ከ፫፻፶ በላይ ምዕመናን በጉባኤው እንደተሳተፉ ለመረዳት ችለናል።

በአቴና ከተማ የተካሄደውን ጉባኤ ኪዳን ጸሎት አድርሰው ባርከው የከፈቱት ቀሲስ ዶ/ር አየለ ወ/ጻድቅ፣ ቀሲስ ሰሎሞን ገ/መድህን እና መሪጌታ ዶ/ር መርዓዊ መለሰ ምዕመናን ለቤተ ክርስቲያናቸው አገልግሎት እንዲተጉ ምክራቸውን አስተላልፈዋል።

በስዊዘርላንድ የተካሄደውን ጉባኤ በጸሎት ባርከው የጀመሩት በስዊዘርላንድ የኢ///ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ኃይለ ጊዮርጊስ ባስተላለፉት ቃለ ምዕዳን ይህ መርሐግብር አንዲሳካ ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው ምዕመናንም ገዳማትን ለመርዳት የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው አንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

ማእከሉ ሁሉም ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄዱ አስተዋጽኦ ላደረጉት በስዊዘርላንድ የጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እና በግሪክ የአቴና ምክሐ ደናግል ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ሰባካ አስተዳደር ጉባኤዎች እንዲሁም በጉባኤው ላይ በመገኘት ድጋፋቸውን ላደረጉ ምዕመናን ሁሉ ምስናጋውን ያቀርባል።

በጀርመን ሀምቡርግ ከተማ ዐውደ ርእይ ተካሄደ

በጀርመን ቀጣና ማእከል

ሰኔ 3 ቀን 2007 ዓ.ም.

በጀርመን ሀገር በሀምቡርግ ከተማ ግንቦት ፳፱ እና ፴ ፳፻፯ ዓ.ም. ”ለሁለንተናዊ የቤተክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል መሪ ቃል የዐውደ ርእይ እና የስብከተ ወንጌል መርሐግብር ተካሄደ። ዐውደ ርእዩን በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ከሀምቡርግ ደብረ መድኃኒት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን መርሐግብሩን የከፈቱት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ብርሃነ መስቀል ተድላ ናቸው።

Hamburg-2

 

Read more

ማኅበሩ ስብከተ ወንጌል በአውሮፓ ሊያካሂድ ነው

ግንቦት 30 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማዕከል ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል በየዓመቱ በምዕራባውያኑ የበጋ ወቅት የሚያካሂደውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀምር አስታወቀ።

Read more

በፓሪስ የደ/ም/ቅ/ማርያም ቤተክርስቲያን የምሥረታ በዓል ብጹዕ አቡነ ዮሴፍ በተገኙበት ተከበረ

በፈረንሳይ ግንኙነት ጣቢያ

ግንቦት 27 ቀን 2007 ዓ.ም.

በፈረንሳይ ሀገር የመጀመሪያ የሆነችው በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የደ/ም/ቅ/ማርያም ቤ/ክ ፲ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓል እና የንግሥ በዓል ከግንቦት ፳፩ እስከ ፳፫ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. በድምቀት ተከበረ። በመጀመሪያ ጥቂት ምእመናን በእመቤታችን በቅድስት ማርያም ሥም በጽዋ ማኀበር ተሰባስበው ለብዙ ዓመታት ከቆዩ በኋላ በ፲፱፻፺፯ ዓ.ም. ግንቦት ወር በወቅቱ የአውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነበሩት አቡነ ዮሴፍ መልካም ፍቃድ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም በመባል ቤተክርስቲያኗ ተመሠረተች፡፡

paris-10-1

Read more

በሀገረ ጀርመን በርሊን ከተማ የቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ

ግንቦት 26 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ፣ምስራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የበርሊን ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን የተገዛው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ግንቦት 23 ቀን 2007 ዓ.ም ተከበረ፡፡

berlin-church-1

Read more

በጀርመን ሙኒክ ዐውደ ርእይ ተካሔደ

በጀርመን ማእክል

ግንቦት 20 ቀን 2007 ዓ.ም.

በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ግንቦት ፲፭ እና ፲፮ ፳፻፯ ዓ.ም. በጀርመን ሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ”ለሁለንተናዊ የቤተክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል ርዕስ የዐውደ ርእይ እና የስብከተ ወንጌል መርሐ ግብር አካሄደ::

munich-exh-1

Read more

፲፭ ኛው የአውሮፓ ማዕከል ጠቅላላ ጉባዔ ሊካሄድ ነው

ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማዕከል ፲፭ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በጀርመን ሀገር ፍራንክፈርት ከተማ ሊያካሂድ ነው። ከሰኔ ፳፮ እስከ ፳፰ ቀን ፳፻፯ዓ.ም. በሚቆየው በዚህ ጉባዔ፦

  • የደቡብ ፣ የደቡብ ምሥራቅ እና የደቡብ ምዕራብ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ እና የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ
  • የሰሜን ምዕራብ ሀገረ ስብከት ተወካይ
  • በጀርመን የሚገኙ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና አባቶች
  • በተለያዩ የአውሮፓ ሃገራት የሚኖሩ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች እንደሚሳተፉበት ይጠበቃል።

Read more

ብፁዕ አቡነ ሙሴ የትንሣኤን በዓል አስከመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

ሚያዚያ 04 ቀን 2007 ዓ.ም.

የደቡብ፣ ደቡብ ምሥራቅ እና ደቡብ ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ የትንሣኤን በዓል አስከመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው ያስተላለፉትን መልእክት ከዚህ በታች ይመልከቱ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

 

በጀርመን ሀገር 2ኛው የሐዊረ ሕይወት ጉዞ ተካሄደ

በአውሮፓ ማዕከል መገናኛ ብዙኀን እና ቴክኖሎጂ አገልግሎት ክፍል

መጋቢት 16 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማዕከል የጀርመን ቀጣና ማዕከል አዘጋጅነት የሐዊረ ሕይወት (የሕይዎት ጉዞ) መርሐ ግብር ከመጋቢት 11 እስከ 13 /2007ዓ.ም በክሩፈልባክህ (Kroeffelbach) ከተማ በሚገኘው በቅዱስ እንጦንስ የግብፅ ገዳም (Sankt-Antonius Kloster) ለሁለተኛ ጊዜ ተካሄደ። በመርሐ ግብሩ ላይ ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች የመጡ ከ200 በላይ ምዕመናን ተሳትፈውበታል::

fft st Antonie monastry

የጉባኤው ተሳታፊዎች አርብ ምሽት 1 ሰዓት ተኩል ላይ ከፍርንክፈረት 64.5 ኪ.ሜ ላይ እርቀት በሚገኘው የቅዱስ እንጦንስ የግብፅ ገዳም የተገኙ ሲሆን፤ የገዳሙ አባቶችም የመጣውን እንግዳ በትህትና በመቀበልና ለሁሉም የማረፊያ ቦታ ሰጥተዋል።

Read more