የአውሮፓ ማእከል ፲፮ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሔደ

በአውሮፓ ማእከል ኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል

ሐምሌ 15 ቀን 2008 ዓ.ም.

ገገገገገ-1-450x252

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ፲፮ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከሐምሌ ፩-፫ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በስዊድን አገር ስቶክሆልም ከተማ ተካሔደ።

በጠቅላላ ጉባኤው በተለያዩ የአውሮፓ አገሮች የሚኖሩ ከሰባ በላይ የማእከሉ አባላት፤ የዋናው ማእከልና የሰሜን አሜሪካ ማእከል ተወካዮች፤ እንደዚሁም ጥሪ የተደረገላቸው ካህናትና ምእመናን ተሳትፈዋል።

Read more

በጀርመን ድሶልዶርፍ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ።

በጀርመን ን/ማእከል ኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል

ግንቦት 24 ቀን 2008 ..

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በጀርመን ድሶልዶርፍ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሙሴ ሚያዚያ 16 ቀን 2008 .. በእለተ ሆሳዕና ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ።

Read more

ሀገረ ስብከቱ የመጀመሪያውን “ዝክረ ቅዱስ ያሬድ“ መርሐግብር አካሄደ

በጀርመን ን/ማእከል ኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል

ግንቦት 20 ቀን 2008 ..

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ፣ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የቤተ ክርስቲያናችን የዜማ አባት የሆነውን ቅዱስ ያሬድን ሕይወቱን እና ሥራዎቹን የሚዘክር “ዝክረ ቅዱስ ያሬድ“ የተሰኘ መርሐግብር በጀርመን ካርልስሩኸ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ከግንቦት 12-14 2008 ዓ.ም. በደማቅ ስነ ሥርዓት አከበረ። በሀገረ ስብከቱ አስተባባሪነት እና በካርልስሩኸ ም/ቅ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅነት በቀረበው መርሐግብር ላይ ከተለያዩ ሃገራት የተጋበዙ መምህራን፣ ጥናት አቅራቢዎች፣ በጀርመን እንዲሁም በፈረንሳይ ፓሪስ ያሉ የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪዎች፣ ምእመናን እና መዘምራን እንዲሁም ጀርመናዉያን እንግዶች በአጠቃላይ 400 የሚደርሱ ታዳሚዎች ተገኝተዋል።

Read more

የጀርመን ንዑስ ማእከል 3ኛውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር አካሔደ

በጀርመን ን/ማእከል ኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል

ሚያዚያ 17 ቀን 2008 ..

germany-3-hhበማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል የጀርመን ንዑስ ማእከል 3ኛውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በጀርመን ክሮፍልባህ ከተማ በሚገኘው ቅዱስ እንጦስ


የግብጽ ገዳም ከሚያዝያ 7- 9 ቀን 2008 ዓ.ም አካሔደ።

ሚያዝያ 7 ቀን 2008 ዓ.ም የመርሐ ግብሩ የመጀመሪያ ቀን የካርስሩህ ምእራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና የክሮንበርግ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በሆኑት በመልአከ ስብሐት ተክሌ ሲራክ የመክፈቻ ጸሎት የተጀመረ ሲሆን፣ በጀርመን ንዑስ ማእከል ሰብሳቢ አቶ ወርቁ ዘውዴ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ተላልፏል፡፡ በመቀተልም የወንጌል ትምህርት በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ተሰጥቷል፡፡

Read more

በጀርመን የክሮንበርግ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ።

በጀርመን ንዑስ ማእከል

የካቲት 13 ቀን 2008 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ፣ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የክሮንበርግ(ጀርመን) ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሙሴ የካቲት 6 ቀን 2008 ዓ.ም. ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል። የቤተክርስቲያኑ መመሥረት በፍራንክፈርትና አካባቢው ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ በዓታ ለማርያም የፅዋ ማኅበርን በማቋቋም ተሰባሰበው ይገለገሉ በነበሩ ምዕመናን ጥረት የተጀመረ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ውጤት መሆኑ በዕለቱ ተገልጸል።

pic2

ይህ ለፍራንክፉርት ከተማ አቅራቢያ በምትገኘው በክሮንበርግ ከተማ የተተከለው ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በጀርመን አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ በኢ//// አብያተ ክርስቲያናት ቁጥር አሥራ ሦስት አድርሶታል።

Read more

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ጽ/ቤት

ታህሳስ 3 ቀን 2008 .

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ መስጠት ያስችለው ዘንድ በመደበኛነት የሚያገለግል የጽ/ቤት ረዳት ሆኖ እገዛ የሚሰጥ አገልጋይ ይፈልጋል፡፡

Read more

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ምሥራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት”የግብጽ እና የኢትዮጵያ ሲኖዶስ ተቋቋመ” ተብሎ እየተናፈሰ ስላለው አሉባልታ መግለጫ ሰጠ።

ገረስብከቱ በቅርቡ የተሳካ ዓመታዊ ስብሰባ፣ የትምህርተ ወንጌልና የዐውደ ጥናት ጉባኤ አካሂዷል።

በጀርመን ንዑስ ማእከል

መስከረም 11 ቀን 2008 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ምሥራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን “በጀርመን የሆክስተር ከተማ ነሐሴ 14 ቀን 2007 ዓ.ም የግብጽ እና የኢትዮጵያ ሲኖዶስ ተቋቋመ” ተብሎ እየተናፈሰ ነው ስላለው አሉባልታ መግለጫ አወጣ:: ሀገረ ስብከቱ መግለጫውን ያወጣው የሐሰት መረጃው ለጥቂት ግለሰዎች በኢሜይል እና ዓለሙ አምላኩ በተባለ የብዕር ስም ጎልጉል በተባለ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራጨ መገኘቱን ምክንያት በማድረግ እንደሆነ ጠቅሶ በተለይም ሀሰተኛው ወሬ በማጠቃለያው “ሦስተኛ ሲኖዶስ ተቋቋመ፤ ዳግመኛ የግብጽ ተገዢዎች ልንሆን ነው፤ ሊቀ ጳጳሱ የአጥቢያ አስተዳዳሪዎችን በተለይም 30 ዓመት ያስተዳደሩትን ሊቀ ካህናት ሳያማክሩ ቤተ ክርስቲያኒቱን ችግር ውስጥ ከተቷት፤ የመንግሥት እጅ አለበት ወዘተ..” የሚል ከእውነት የራቀ አሉባልታ ዘገባ እንደተደረገ ሀገረ ስብከቱ ደረሶበት እንደሆነ ይገልጻል።

Read more

ሀገረ ስብከቱ የመጀመሪያውን ልዩ የትምህርተ ወንጌል ጉባኤና ዐውደ ጥናት እንደሚያካሂድ አሳወቀ፡፡

በወርቁ ዘውዴ

ነሐሴ 19 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የደቡብ፣ ምሥራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ከነሐሴ ፴ እስከ ጷጉሜን ፩ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት በሚገኝበት በጀርመኗ ሮሰልሳይም ከተማ የትምህርተ ወንጌል ጉባኤ እና ዐውደ ጥናት ለማካሄድ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አሳወቀ፡፡ ሀገረ ስብከቱ በአዲስ መልኩ ተዋቅሮ የመንበረ ጵጵስና መቀመጫውን በጀርመን ካደረገበት ጊዜ አንስቶ አስተዳደራዊ መዋቅሩን በማጠናከር የቤተ ክርስቲያኗን መንፈሳዊ አገልግሎት የሚደግፍና የሚያግዝ ጠቃሚ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡

Read more

በፓርማ አውደ ርእይ ተካሄደ

በጣሊያን ንዑስ ማእከል

ሐምሌ 26 ቀን 2007 ዓ.ም.

የፓርማ ቤዛ ብዙኃን ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ጋር በመተባበር ያዘጋጀው አውደ ርእይ በጣሊያን ፓርማ ከተማ ተካሄደ።parma-1

Read more

በዴንማርክ ዐውደ ርእይ ተካሄደ

በዴንማርክ ግኑኝነት ጣቢያ

ሐምሌ 10 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማዕከል የዴንማርክ ግንኙነት ጣቢያ ከዴንማርክ የደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባበር በኮፐንሃገን ከተማ ዐውደ ርእይ አካሄደ። ዐውደ ርእዩ በመልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ጸሎት እና የመግቢያ ንግግር እንዲሁም ለአውሮፓ ማዕከል ፲፭ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከዋናው ማዕከል ተወክለው በመጡት በአቶ ፋንታሁን ዋቄ ለሕዝቡ ክፍት ሆኗል። ዐውደ ርእዩ የተካሄደው ሐምሌ ፫ እና ፬ ፳፻፯ ዓ.ም. ሲሆን በሁለቱ ቀን መርሐ ግብር ከመቶ ሰው በላይ ተገኝቷል።dk exhibition 1

Read more