ደብረ ዘይት

ደብረ ዘይት ማለት የወይራ ዛፍ ያለበት ተራራ ማለት ነው፡፡ቦታው ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ የሚገኝ የወይራ ዛፍ የበዛበት ተራራ ሲሆን ስሙም ከወይራ ዛፉ:-ደብረ ዘይት (የወይራ ዛፍ ተራራ) በመሰኘት ተገኝቷል። በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ደብረ ዘይት በዓል ሆኖ የሚከበርበት ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረዘይት ተራራ ላይ ሳለ ለቅዱሳን ደቀመዛሙርቱ ስለ ዓለም ፍጻሜ እና ስለ ዳግም ምጽአቱ ስላስተማራቸዉ በጌታችን ትምህርት መሰረት ነገረ ምጽአቱን (የመምጣቱን ነገር) እንድናስታዉስ ወይም እያሰብን እንድንዘጋጅ ለማድረግ ነዉ።debre Zeyt

Read more

የጥምቀት አስፈላጊነት

በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከኒቂያ ጉባኤ በኋላ ከተነሱት አባቶች አንዱ “በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም” ራእይ ፳፥፮ የሚለውን የወንጌላዊው ዮሐንስን አባባል በተረጎመበት የእግዚአብሔር ከተማ በሚለው መጽሐፉ ላይ ፊተኛው ትንሣኤ የተባለው ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና የምናገኝበት ጥምቀት እንደሆነ ገልጿል (De Civitate Dei,xx,6)።

Read more

“ተወልደ ኢየሱስ በቤተ ልሔም ዘይሁዳ”(ቅ. ያሬድ)

ታኅሣሥ 28 ቀን 2004 ዓ.ም. 

በቀሲስ ደመቀ አሸናፊ


በጌታችንና በአምላካችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተደረገልን ፍፁም ሥርየትና እርቅ ግልጥ ሆኖ የተጀመረው በነገረ ልደት ነው። የጌታችን ልደት በነገረ ድኅነት ትልቅ ስፍራ የያዘና እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ፍፁም ልዩ መሆኑን ያሳየ ነው። መስተፃርራን የነበሩ ሰማይና ምድር፣ ሰውና መላእክት በአንድነት ለምስጋና ታድመዋል። የእረኞች አንደበት ከመላእክት ጋር ለሰማያዊ ምስጋና ብቁ የሆነበት፤ ግዕዛን የሌላቸው እንስሳት ሰራኢ መጋቢያችን፣ በዘባነ ኪሩቤል በሰማያት የምትገለጥ አንተ ነህ ሲሉ እስትንፋሳቸውን የገበሩለት፤ የምድር ነገስታት በሥልጣንህ ሽረት በመንግሥህ ህልፈት የሌለብህ የነገስታት ንጉሥ አንተ ነህ ሲሉ ወርቅን ለመንግሥቱ፣ ዕጣንን ለክህነቱ፣ ከርቤን ለህማሙ ዕጅ መንሻን ያበረከቱለት፤ ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ከጻድቁ ዮሴፍ ጋር ያን ልዩ ክብር የዩበት፤ ይህ ልደት በእውነት ልዩ ነው።

Read more

ሠለስቱ ደቂቅ

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች?ደህና ናችሁ ልጆች? ዛሬ ስለ ሦስቱ ልጆች ታሪክ እንነግራችኋለን በደንብ ተከታተሉን እሺ፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፣ በድሮ ጊዜ እግዚአብሔርን የማይፈራ ናቡከደነፆር የሚባል የባቢሎን ንጉሥ ነበር፡፡ይህም ንጉሥ ከወርቅ የተሰራ ትልቅ ጣኦት አቁሞ ሕዝቡንም ሁሉ ሰበሰበና ለጣኦቱ እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ ለጣኦት ያልሰገደ ግን በእሳት ውስጥ ይጣላል ብሎ አዋጅ አስነገረ፡፡

Read more

የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን

መግቢያ

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በተለያየ ጊዜ ካህናት እና ምእመናን የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት በተባለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዴት ሊኖሩ እንደሚገባ ድርሻቸውም ምን እንደሆነ ያስተምራቸው ነበር:: ለምሳሌ የመንፈስ ልጁ የሆነ ቅዱስ ጢሞቴዎስን በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት ሲኖር ምን ማድረግ እንዳለበት እንዲህ በማለት መክሮታል:-“በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዐምድና መሠረት የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው::” (1ጢሞ 3፥15)

Read more

የጌታችን ትንሣኤ

ልጆች ስለ ጌታ ከሞት መነሣት ሰምታችሁ ታውቃላችሁ? እስቲ ትንሽ ስለ ትንሣኤው ልንገራችሁ:: ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ዓርብ ቀን በሐሰት ሰቅለው ከገደሉት በኋላ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ሥጋውን ከመስቀል ላይ አውርደው በንጹህ በፍታ ገንዘው በአትክልት ቦታ በሚገኝ አዲስ መቃብር ውስጥ ቀበሩት። ትልቅ ድንጋይም አንከባለው የመቃብሩን አፍ ዘጉት። በአይሁድ የታዘዙ ብዙ ጭፍሮች (ወታደሮች) የጌታችንን መቃብር ይጠብቁ ነበር።

ልጆች፣ ጌታችን ከሞት ሲነሣ የታዩትን ድንቃ ድንቅ ነገሮች ታውቃላችሁ? Read more

ኢትዮጵያዊዉ ጃንደረባ

በዓለም የክርስትና ታሪክ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቀዳሚውን ስፍራ የያዘችና ሐዋርያዊት ለመሆንዋ ምስክር ከሚሆኑ ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል ባኮስ ቀዳማዊ ነው። ኢትዮጵያውያን ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ ሕዝበ እግዚአብሔር ከሚባሉ እስራኤል ጋር በአምልኮተ እግዚአብሔር የሚኖሩ ሕዝብ ስለመሆናቸው ቅዱስ መጽሐፍ ይመሰክራል። አያሌ የታሪክ መዛግብትና የአርኪዮሎጂ ምርምር ውጤቶችም ይህንን እውነት ያረጋግጣሉ። እኛም በዚህ የቅዱሳን ታሪክ ዓምድ፣ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ”በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም” ማቴ፭፥፲፬ እንዳለ፤ በረከቱና አርአያነቱ ለትውልድ ይተርፋል በማለት የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ታሪክ ይዘን ቀርበናል። የቅዱሳን አማላጅነትና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
Read more

ዕውቀት እንዳይሞት

ቤተ ክርስቲያን ሰማይና ምድር ከመፈጠራቸው በፊት ነበረች። ዓለማት ከተፈጠሩ በኋላ በዓለመ መላእክት፣ በዓለመ መሬት በሕገ ልቡና እና በሕገ ኦሪት እግዚአብሔር በመረጣቸው ነቢያትና ካህናቱ አማካኝነት ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ስታገናኝ ኖራለች። በዘመነ ሐዲስ ደግሞ በደመ ክርስቶስ ተዋጅታ ሕገ ወንጌልን ስትናኝ እና አምልኮተ እግዚአብሔርን ስታስፋፋ ኖራለች። በነዚህ አዝማናት ሁሉ ስለ እርሷ ሳይፈሩና ሳያፍሩ አንገታቸውን ለሰይፍ፣ ጀርባቸውን ለግርፋት፣ እግራቸውን ለሰንሰለት የሰጡላት፣ በብዙ መከራዎች የተጋደሉላትን አበው፣ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ሰማዕታትን እና በእነርሱ መንገድ የተጓዙ ብዙ ሊቃውንትን አፍርታለች (ዕብ ፲፩)።
Read more

ሕይወት በባዕድ ምድር (፪ጴጥ. ፪፥፰)

የርዕሳችን መነሻ የሆነው በ፪ኛ ጴጥሮስ ምዕራፍ ፪ ላይ የምናገኘው ታሪክ ነው። “ጻድቅ ሎጥም እያየና እየሰማ፣ አብሮአቸውም እየኖረ በክፉ ሥራቸው ዕለት ዕለት ጻድቅት ነፍሱን ያስጨንቃት ነበር።” ፪ጴጥ. ፪፥፰

ሎጥ ኃጢአትን የዕለት ከዕለት ተግባራቸው ካደረጉ ሰዎች ጋር ለመኖር የተገደደው በዘፍ ፲፫ ላይ እንደምናነበው ከአጎቱ ከአብርሃም ጋር ይኖርበት የነበረው ቦታ ስለጠበባቸው በእረኞቻቸው መካከልም እየተፈጠረ የነበረው ጥላቻ ወደ እነርሱ እንዳይጋባ ራቅ ወዳለ ቦታ መሄድ ስለነበረበት ነበር። ለመለያየት ሲወስኑም ለሎጥ እንዲመርጥ ዕድል በተሰጠው ጊዜ የመረጣት ውሃ የሞላባትን ለምለሟን ሰዶምን ነበር። ሎጥ ግን በጎረቤቶቹ መካከል እየኖረ ዕለት ዕለት የሚሠሩትን ሥራ እያየና እየሰማ

Read more