ደብረ ዘይት

በአባ ዘሚካኤል ደሬሳ

መጋቢት 24 ቀን 2008 ዓ.ም.

ደብረዘይት የዓቢይ ጾም እኩሌታ ነው በእለቱም ስለ ዳግም ምጽአት ይነገራል። ስለ ምጽአት ነቢዩ ዘካርያስ «በዚያን ቀን እግሮቹ በኢየሩሳሌም ትይዩ በምሥራቅ በኩል ባለው በደብረ ዘይት ላይ ይቆማሉአምላኬ እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ ጋር ይመጣልአንድ ቀን ይሆናል…. በዚያም ቀን የሕይወት ውኃ ከኢየሩሳሌም ይወጣል፤ እኩሌታው ወደ ምሥራቁ ባሕር እኩሌታውም ወደ ምዕራቡ ባሕር ይወርዳል።» (ዘካ ፲፬ ) በማለት አስቅድሞ ትንቢት ተናግሯል። አምላክ በዚህ ትንቢት እና በሌሎች ነቢያት ያናገረውን እርሱ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ ላይ የዳግም ምጽአት ምልክቶችን እና አመጣጡን ከፍርዱ ሂደት ጋር በግልጽ አስተምሯል። ይህንንም ሁሉ የተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደብረ ዘይት እለት ስትዘከረው ኖራ በምጽአት ቀን ተስፋዋን መንግሥተ ሰማያትን ትረከባለች:: በመሆኑም በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እንደተለመደው በዚህ የደብረ ዘይት ሳምንት ጽሑፍ ስለ ደብረ ዘይት ስለምጽአት ምልክቶች ስለምጽአት እና ተስፋው እንዘከራለን

Read more

መጻጒዕ (ዮሐ. ፭፥፲፫)

በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ

መጋቢት 18 ቀን 2008 ዓ.ም

የነፍሳችንን ማሠሪያ እንዲፈታና ዓለሙን ከተያዘ የኃጢአት በሽታ እንዲያድን ለቤዛነት፤ እንዲሁም የመልካምና የበጎ ምግባራት ሁሉ አብነት ሆኖ በሥራና በቃል እንዲያስተምር ወዳለንባት ምድር በሥጋ ቅድስት ድንግል ማርያም ወረደ ተወለደ:: ቤተክርስቲያናችን በአራተኛው ቢይ ጾም ሳምንት እግዚአ ለሰንበት ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተሳይዳየፈጸመውን ተአምራት መጻጒዕ ብላ ሰይማ ስበዋለች። በዕለቱም በዮሐንስ ወንጌል አምስተኛው ምዕራፍ የተቀመጠው ታሪክ በልዩ ልዩ ኅብረ ምሥጢር ተገናዝቦ በሊቃውንቱ ይነገራል።

መጻጒዕ ለ፴፰ ዓመት በአልጋው ላይ ሆኖ ምሕረትን ሲጠባበቅባት የኖረባት ስፍራንቤተ ሳይዳትባላለች በቅዱስ መጽሐፍ የሥፍራዎችን ስያሜ ስንመረምር በይሁዳና በገሊላ ለሚገኙ ሁለት የተለያዩ ግዛቶች በተመሳሳይ አገባብቤተ ሳይዳየሚል መጠሪያ ተሰጥቷቸው እናገኛለን። በሁለቱ አውራጃዎች (ይሁዳና ገሊላ) ሥርቤተ ሳይዳበሚል የተጠቀሱት ሥፍራዎች በትርጉም ፊደላቱ ያለአገባብ መሰደር ከወለዱት የሞክሼነት ስህተት (Metathetical Corruption) የተገኘ ክፍተት እንጂ ቦታዎቹስ በጥንታዊቷ የእስራኤል ግዛት ከመገኘታቸው ውጪ ምንም የሚያገናኛቸው መልክአ ምድራዊ ኩነት የለምጲላጦስ ጰንጤናዊ መልአከ ይሁዳ ወሄሮድስ ንጉሠ ገሊላ” (ሉቃ· ፫፥፩) እንዲል የግዛቶቹ አገረ ገዢዎችም እንዲሁ ለየቅል ነበሩ። አገባቡን አካቶ ለመረዳት እንዲያመች የሁለቱንም መካናት ከተማና መንደር ለይቶ ማወቁ ተገቢ ነው።

Read more

ምኵራብ

ቀሲስ ኃይለኢየሱስ ተመስገን


መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓ.ም

ከሁሉ አስቀድሞ ሃይማኖትን መመስከር እንዲገባ ቅድመ ዓለም ከእግዚአብሔር አብ ያለ እናት አካል ዘእምአካል ባህርይ ዘእምባህርይ የተወለደ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አካላዊ ቃል ድህረ ዓለም ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መለወጥ ሳያገኛት ዘር ምክንያት ሳይሆን ከስጋዋ ስጋ ከነፍ ነፍስ ነስቶ የተወለደ ወልደ እግዚአብሔር ወልደ ማርያም በተዋህዶ ከበረ“ይደልዎነ ንምን ከመ ቦቱ ለወልደ እግዚአብሔር ክልኤቱ ልደታት ቀዳማዊ ልደቱ እም እግዚአብሔር አብ እምቅድመሉ መዋዕል ወዳግማዊ ልደቱ እም እግእዝትነ ቅድስት ድንግል ማርያም በደራዊ መዋዕል” ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ ፴፬ ቁጥር ክፍል ብለን በማመን እንደ አባቶቻችን ረድኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ አድርገን ስለ ምኵራብ እንማራለን የምናነበውን ለበረከት ያድርግልን አሜን።

Read more

ዘወረደ

ዲያቆን ስመኘው ጌትዬ

የካቲት 26 ቀን 2008 ዓ.ም.

እንኳን ለዓቢይ ጾም በሰላም አደረሰን። የ፳፻፰ (2008) . ዓቢይ ጾም የካቲት ፳፰(28) ቀን ተጀምሮ ሚያዝያ ፳፫ (23) ቀን ይፈጸማል። ይህ ጾም 8 ታላላቅ ሳምንታት የተከፋፈለ ሲሆን እነርሱም ዘወረደ፣ ቅድስት፣ ምኲራብ፣ መጻጒዕ ደብረዘይት፣ ገብርኄር፣ ኒቆዲሞስ፣ እና ሆሳዕና ይባላሉ፡፡ በዚህ ጾም ውስጥ በአጠቃላይ ጾመ እግዚእነ (የጌታችን ጾም) አርባውን ቀን ሲይዝ የመጀመሪያው ሳምንት ጾመ ሕርቃል እና የመጨረሻው ሳምንት የጌታን ሕማማት የምናስብበት ሰሙነ ሕማማት የቀረውን ክፍል ይይዛሉ፡፡

ዛሬ የመጀመሪያውን ሳምንት ወይም ዘወረደ የተባለውን ጾም ስያሜውን እና ምስጢሩን በታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ትምህርት እንዴት እንደተገለጠ እናያለን፡፡ የብሉያት እና የሐዲሳት መጽሐፍት ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ከጸዋትወ ዜማ መጽሐፍቱ አንዱ በሆነው የድጓ ክፍል ጾመ ድጓ (በጾም ስለሚደረስ ጾመ ድጓ ተብሏል) ስለ ጾም ብዙ ጽፏል።ከዘወረደ ጀምሮ ያሉት ስምንቱም ሳምንታት ስያሜያቸውን ያገኙት ከጾመ ድጓ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በተለይ ዋዜማ ክፍሉ ላይ ያሉትን የመጀመሪያ ቀለማት በመምረጥ የየሳምንታቱን ስያሜዎች አስገኝቷል፡፡ በዘወረደ ድርሰቱ ቅዱስ ያሬድ በጾም ልናስባቸው እና ልናከናውናቸው የሚገቡንን ነገሮች ከሥነምግባር፣ ከጸሎት፣ ከቤተክርስቲያን፣ ከመስቀሉ አንፃር እየሆነ ይነግረናል፡፡ ዛሬ በዘወረደ ድርሰቱ ከተገለጡት በጥቂቱ እያነበብን እንማማራለን።

Read more

የገና በዓል በቅዱስ ላሊበላ

በቀሲስ መንግስቱ ጎበዜ

ታህሳስ 27 ቀን 2008 ዓ.ም

በቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን በድምቀት ከሚከበሩት የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓበይት በዓላት መካከል ገና (የልደት) በዓል አንዱ ነው።ይህ በዓል ሰማይና መሬት የታረቁባት፣ ሰው እና መላእክት በአንድነት የዘመሩበት ከሁሉም በላይ አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲጠበቅ የነበረው የአዳም ተስፋ የተፈፀመበት፣ አምላክ የአምላክ ልጅ በግሩም ተዋህዶ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ የተወለደበት ታላቅ የደስታ ቀን ነው።

Read more

ጾም በስደት ሀገር

በቀሲስ ለማ በሱፈቃድ

ሐምሌ 30 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሰባት አጽዋማት አሉ :: ከእነዚህም አንዱ ጾመ ፍልሰታ ነው:: ጾም ማለት በታወቀ ወራት ሳምንታት እና ዕለታት እስከ ጾሙ ፍጻሜ ድረስ ከተከለከሉ ጥሉላት ምግቦችና መጠጦች ወይም የእንስሳት ውጤቶች ሥጋ ወተትና ከመሳሰሉት መከልከል ሲሆን፣ ከዚያ ውጪ የሆኑ ምግቦች ለተወሰነ ሰዓት ብቻ መከልከል ነው :: ‘’ ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም ሥጋና ጠጅም በአፌ አልገባም ሦስቱም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ዘይት አልተቀባሁም’’ /ዳን .. /። ‘’ጾምሰ ተከልዖተ ብእሲ እመብልዕ በጊዜ እውቅ ‘’ /ፍትሐ ነገሥት አንቀጸ ጾም ተመልከቱ/። በሌላ መልኩ ደግሞ ጾም ማለት በዓይናችን በእጃችን በእግራችን በአንደበታችንና በመሳሰሉት የሰውነት ክፍሎቻችን ሁሉ ሳይቀር የምንጾመው ነው:: “ስንጾም አንደበታችንም ከማይገቡ ንግግሮችና ከነቀፋዎች ይጹም::’’ /.ዮሐንስ አፈ ወርቅ በእንተ ምክንያተ ሐውልታት ፫ ;.፲፪”/:: ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው «ይጹም ዐይን፥ ይጹም ልሳን፥ ዕዝንኒ ይጹም እምሰሚዐ ህሱም በተፋቅሮ፤ በፍቅር በመጽናት ዓይን ክፉ ነገርን ከማየት ይጹም፣ አንደበትም ክፉ ከመናገር ይጹም፣ ጆሮም ክፉ ከመስማት ይጹም” ብሎ ገልጾታል።

Read more

ደብረ ዘይት

በአባ ዘሚካኤል ደሬሳ

መጋቢት 4 ቀን 2007 ዓ.ም.

ደብረዘይት የዓቢይ ጾም እኩሌታ ነው ። በእለቱም ስለ ዳግም ምጽአት ይነገራል። ስለ ምጽአት ነቢዩ ዘካርያስ «በዚያን ቀን እግሮቹ በኢየሩሳሌም ትይዩ በምሥራቅ በኩል ባለው በደብረ ዘይት ላይ ይቆማሉአምላኬ እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ ጋር ይመጣል አንድ ቀን ይሆናል…. በዚያም ቀን የሕይወት ውኃ ከኢየሩሳሌም ይወጣል፤ እኩሌታው ወደ ምሥራቁ ባሕር እኩሌታውም ወደ ምዕራቡ ባሕር ይወርዳል።» (ዘካ ፲፬ ፥ ፬) በማለት አስቅድሞ ትንቢት ተናግሯል :: አምላክ በዚህ ትንቢት እና በሌሎች ነቢያት ያናገረውን ፣ እርሱ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ ላይ የዳግም ምጽአት ምልክቶችን እና አመጣጡን ከፍርዱ ሂደት ጋር በግልጽ አስተምሯል። ይህንንም ሁሉ የተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደብረ ዘይት እለት ስትዘከረው ኖራ በምጽአት ቀን ተስፋዋን መንግሥተ ሰማያትን ትረከባለች:: በመሆኑም በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እንደተለመደው በዚህ የደብረ ዘይት ሳምንት ጽሑፍ ስለ ደብረ ዘይት ፣ ስለምጽአት ምልክቶች ፣ ስለምጽአት እና ተስፋው እንዘከራለን ።

Read more

ጾመ ነነዌ

ኤርምያስ ልዑለቃል (ዶ/ር)

ጥር 26 ቀን 2007 ዓ.ም. 

የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስተው ይፈርዳሉ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡” (ማቴ ፲፪፥፵)

ይህንን የተናገረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ጌታችን ለዚህ ትምህርቱ መነሻ ያደረገው የጻፎች የፈሪሳውያንን ጥያቄ ነው፡፡መምህር ሆይ ከአንተ ምልክት ልናይ እንወዳለን” ቢሉትክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም ዮናስ በአሳ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሌሊት አንደነበረ የሰው ልጅም በምደር ልብ ሦስት ቀንና ሌሊት ይሆናል፡፡የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስተው ይፈርዳሉ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡ እነሆ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ” ብሏቸዋል፡፡ (ማቴ ፲፪፥፵) ጻፎችና ፈሪሳውያን ምልክት መጠየቃቸው ይገርማል! የተሰጣቸውን ምልክት ሳይጠቀሙ እና በሚያዩአቸው ተአምራት ሳያምኑ ሌላ ምልክት መሻታቸው ይደንቃል! አልተረዱትም እንጂ የእርሱ በመካከላቸው መገኘት በራሱ ምልክታቸው ነበረ::ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋልእነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች” አንዳለ ነቢዩ (ኢሳ ፲፬ ) ሰማያዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ያበሰራት እመብርሃን ምልክታቸው ነበረችበድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች መቤታችን ምልክታቸው ነበረችበጌታችን ልደት ወደ ቤተልሔም ወርደው የዘመሩ ቅዱሳን መላእክትም ምልክቶቻቸው ነበሩየተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው” እያሉ የመጡት ሰብአ ሰገልም ምልክቶቻቸው ነበሩ፡፡ ከዚህም በላይ በመካከላቸው ሆኖ ማየት ለተሳናቸው ዓይን ሲሰጥ መስማት የተሳናቸው እንዲሰሙ ሲያደርግ ለምጻሞችን ሲያነጻ እና ሙታንን ሲያስነሳ እያዩ እንደገና ሌላ ምልክት አምጣ ማለታቸው የሚገርም ነው! ለዚህም ነውክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን ይሻል” ብሎ ወደ ነነዌ ሰዎች ትምህርት የወሰዳቸው፡፡

ነነዌ ማናት?

Read more

ጥምቀት እና በዓለ ጥምቀት

በዲ.ን ዶ.ር አለማየሁ ኢሳይያስ

ጥር 8 ቀን 2007 ዓ.ም.

ጥምቀት

ጥምቀት የሚለው ቃል አጥመቀ (አጠመቀ ወይም ነከረ) ከሚለው የግእዝ ሥርወ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም መጠመቅ ፣ መነከር ፣ መደፈቅ ፣ ውኃ ውስጥ ብቅ ጥልቅ ማለት ነው ። ጥምቀት ከሌሎቹ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን በመጀመሪያ ላይ የሚፈጸም ምሥጢር ሲሆን ያለ ጥምቀት ከሌሎቹ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን መሳተፍ አይቻልም ። (ዮሐ. ፪፥፩-፵፩) በጥምቀት ከእግዚአብሔር በመንፈስ እንወለዳለን፤የልጅነት ፀጋንም እናገኛለን። የነፍስ ድኅነትን ለማግኘትም በጥምቀት የእግዚአብሔርን ልጅነት ማግኘት ግድ ነው ።(ማር ፲፮፥፲፮ ፤ ዮሐ ፫፥፭) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀበትን እለት በታላቅ ድምቀት በየዓመቱ ጥር ፲፩ ቀን እንደምታከብር ይታወቃል። የጥምቀት በዓል አከባበር የሚጀምረው ጥር ፲ ቀን በጾም ሲሆን ይህም እለት ገሀድ በመባል ይታወቃል።ትርጉሙም መገለጥ ማለት ነው። ምክንያቱም ወልድ የተባለ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ ፣ በኋለኛው ዘመን ደግሞ ያለ አባት ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነስቶ፣ ከሁለት አካል አንድ አካል፣ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆኖ ተዋሕዶ ስለተገለጠልን እና በ፴ ዓመቱ በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ተጠምቆ ክብሩንና ጌትነቱን ስለገለጠልን ነው።

Read more

ልዩ ከሆነች ድንግል ማርያም ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይደንቅ

ዲ.ን ብሩክ አሸናፊ

ቀን ታህሣስ 27 ቀን 2007 ዓ.ም.

«ኦ ዝ መንክር ልደተ አምላክ እማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ልዩ ከሆነች ድንግል ማርያም ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይደንቅ» ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ

ይህ ቃል በ፫፻፮ ዓ.ም ገደማ በሜሶጶጣሚያ ውስጥ በምትገኘው በንጽቢን ተወልዶ፣ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ እስኪል ድረስ ጸጋ እግዚአብሔር በዝቶለት እጅግ ብዙ ድርሳናትን የደረሰው፣ በጉባኤ ኒቅያ መምህሩ ከነበረው የንጽቢን ጳጳስ ያዕቆብ ጋር የተገኘው፣ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ እመቤታችንን ባመሰገነበት ውዳሴ ማርያም በተሰኘው መጽሐፉ ላይ ልዩ እና ድንቅ የሆነውን የጌታችንን ልደት አድንቆ በሐሙስ ክፍል ላይ የጻፈው ነው።

Read more