አብርሃ ወአጽብሐ

ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም

ቅዱሳን ነገስታት አብርሃ ወአጽብሐ አባታቸው ታዜር እናታቸው ሶፍያ/አህየዋ/ በቅድስና የሚኖሩ እግዚአብሔርን በቅድስና በንጽህና የሚያገለግሉ ነገር ግን ልጅ ያላገኙ መካኖች ነበሩ። ስለሆነም ጌታ ሆይ ደስ የሚያሰኝህ በትዕዛዝህም የሚኖር ልጅ ስጠን እያሉ እግዚአብሔርን ይለምኑ ነበር፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ስለ እግዚአብሔር ቸርነት ሲነጋገሩ ንግስት ሶፍያ የሐና እመ ሳሙኤልን ጸሎት በመጥቀስ እሷም እንደ ሐና ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን እንድትለምን ንጉሱን ጠየቀችው፡ ንጉሱም “ ኦ ብእሲቶ ሰናየ ኁለይኪ” አንቺ ሆይ መልካም አስበሻል በማለት በምክሯ ተስማምቶ ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን በጸሎት እንድትጠይቅ ፈቀደላት፡፡ ንግስት ሶፍያም የካቲት 18 ቀን ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን መለመን ጀመረች፡፡ ከጸሎቷም ጥቂቱ “ በኪሩቤል ላይ የምትኖር፣ የቀለያትንም (ጥልቅ ባህርንም) የምትመለከት ጌታዬ ፈጠሪዬ ሆይ አቤቱ ጸሎቴንና ልመንያን ስማኝ፣ ልቅሶየንም አድምጥ ቸላ አትበለኝ” የሚል ነበር፡፡

Read more

በክርስቶስ በኲርነት ኹላችን እንነሣለን (፩ኛ ቆሮ፲፭፥፳-፳፪)

በዲ/ን ሰሎሞን አስረስ

ሚያዚያ 11 ቀን 2006 ዓ.ም. 

እግዚአብሔር ሰውን እንደ መላእክት ሕያው ስሙን ሊቀድስ ክብሩን እንዲወርስ እንጂ እንዲታመም እንዲሞት አድርጎ አልፈጠረውም ነበር፡፡ ሞት ግን ሰው በፈቃዱ ያመጣው እንጂ እግዚአብሔር ሰውን ሊሞት አልፈጠረውም ። ጥበበኛው ሰሎሞን ‹‹በሕይወታችሁ ስሕተት ለሞት አትቅኑ፤ በእጃችሁም ሥራ ጥፋትን አታምጡ፡፡ እግዚአብሔር ሞትን አልፈጠረምና፤ የሕያዋንም  ጥፋት ደስ አያሰኘውምና፡፡ ነዋሪ ይሆን ዘንድ ፍጥረቱን ፈጥሮአልና፡-የዓለም መፈጠርም ለድኀነት ነውና በእነርሱም ዘንድ የጥፋት መርዝ አልነበረምና ለሲኦልም በምድር ላይ ግዛት አልነበረውምና፡፡ ጽድቅ አትሞትምና፡፡ ክፉዎች ግን በእጃቸውና በቃላቸው ጠሩት፤ ባልንጀራም አስመሰሉት፡፡ በእርሱም ጠፋ፡፡›› እንዲል። (ጥበብ ፩፥፲፪-፲፯)::

Read more

የመምጣትህና የዓለሙ ፍፃሜ ምልክቱ ምንድን ነው? (ማቴ 24፡4)

መጋቢት 12 ቀን 2006 ዓ.ም. 

መ/ር ሰሎሞን መኩሪ 

በቅዱስ ወንጌል የመምጣትህና የዓለሙ ፍፃሜ ምልክቱ ምንድን ነው? (ማቴ 244) የጠየቁ የእጁን ተአምራት ተመልክተው የቃሉን ትምህርት ሰምተው ሁሉን ትተው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዋለበት የዋሉ ካደረበት ያደሩ ትምህርት ተአምራት ያልተከፈለባቸው ቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት ናቸው፡፡ ርሱም የተናገራቸውን ሰምተው ለብቻቸው ሲሆኑ በሚያድሩበት በደብረዘይት ተራራ ላይ ጌታ ሆይ ንገረን ይህ መቼ ይሆናል የመምጣትህና የዓለሙ ፍፃሜ ምልክቱ ምንድን ነው? ብለው ጠየቁት በዚህ ክፍለ ንባብ ሐዋርያት ሶስት ነገሮችን ጠይቀውታል፡፡

Read more

ዓቢይ ጾም

የካቲት 15 ቀን 2006 ዓ.ም.

በአባ ዘሚካኤል ሬሳ 

እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ለመጾም አደረሳችሁ!!!

ጌታችን መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄደ። አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ጾመ። ከዛም ፈታኝ ዲያብሎስ ቀርቦ በስስት፣ በትእቢትና በፍቅረ ነዋይ ፈተነው። ጌታችንም ፈተናዎቹን በጥበበ አምላክነቱ ድል በማድረግ ድልን ለአዳምና ለእኛ ለልጆቹ ሰጠን (ማቴ. 4፡ 1 – 11)

በቤተ ክርስቲያናችን የትምህርተ ጾም አስተምህሮ መሰረት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾመ ሁዳዴ ትልቁን ስፍራ ይይዛል። ይህም የቀደመው አዳም በጾም ግድፈት ምክንያት ማለትም አትብላ የተባለውን በመብላት ወድቆ፣ተዋርዶ፣ ኃይሉን አጥቶ፣ ዲያብሎስ ሰልጥኖበት፣ ስጋ ፈቃድ አይሎብት፡ የዓለም አምሮት ማርኮት ሞትና የሞት ሞት ሰልጥኖበት ነበረ። ነገር ግን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ተወልዶ፣ በገዳመ ቆሮንቶስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ፣ ሰው በእግዚአብሔር ቃል እንጂ በእንጀራ ብቻ እንደማይኖር አረጋግጦ፣የአዳም ጾም መሻርና የመዋረዱን ክስረት ለመካስ ጌታም ይህን ጾም በመጾም የአዳምን ክብረት መልሶለታል

Read more

እስክመጣ ድረስ ያላችሁን ጠብቁ (ራእ ፪፡፳፭)

በዲ/ን ሰሎሞን መኩሪያ 

ጥቅምት 29 ቀን 2006 ዓ.ም. 

ይህንን ይለ ቃል የተናገረው ቅዱስ እግዚአብሔር በሐዋርያዉና ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ማካነው። ቅዱስ ዮሐንስ ከዓሣ አጥማጅነት ከተጠራበት ጊዜ አንስቶ ጌታችንን እስከ እግረ መስቀል ስ ተከተሎታል፤ በዚያም የጌታችንን መከራ እየተመለከተ ቢያዝንና ቢያለቅስ ይጽናና ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እን እናትህ በማለት የእናትነት ቃል ኪዳን ተቀብሏል። እርሷንም ወደ ቤቱ ወስዶ ፲፭ ዓመት ታጥቆ ልግሏታል።

ስብከተ ኤፌሶን ሂዶ በዚ ወንጌልን ለማስተማር ከጣዖት አምላኪው ንጉስ ድምጥያኖስ ብዙ መከራ ተቀብሏል። በዚያም ለነበሩ ምእመናን የሃይማኖት ጽናትንና መከራ በመቀበል ያስተማረ ሰባት አብያተ ክርስትያናትን ከመሠረተ በሁዋላ ከንጉስ ድምጥያኖስ ግዞት ተፈርዶበት ፍጥሞ ወደ ምትባል ደሴት ግዞ በዚያም በምድርና በሰማይ ያለውን ወደፊትም የሚደረገውን ነገር በራእይ ተገልጾለት ጽፏል። ላም ፺፱ ዓመቱ ሞትን ሳያይ የተሰወረ የቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ ቅዱስ ነው። (ማቴ፲፱ ዮሐ ፲፱፳፮ ዮሐ ፳፩፳፬)

Read more

አቤልና ቃየል (ለልጆች) (ዘፍ.4፣1-15)

 

በአውሮፓ ማዕከል ትም/ እና ሐዋሪያዊ አገልግሎት ክፍል

ጥቅምት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. 

አዳም እና ሔዋን በመጀመሪያ ቃየልን እና አቤልን ወለዱ። አቤልም በግ ጠባቂ ነበረ፤ ቃየል ምድርን የሚያርስ ነበረ። ሁለቱም ካላቸው ነገር ለእግዚአብሔር ስጦታ ወይም መሥዋዕት አቀረቡ። ቃየል ክፉ ልብ ነበረውና እግዚአብሔር አይበላው ብሎ ከአመረተው እህል ጥሩዉን ሳይሆን መጥፎዉ የማይረባውን መናኛውን እህል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አቀረበ። አቤል ልቡ ንፁህ ነበርና እግዚአብሔር ንጹሐ ባህርይ ማለት ነው ሲል ያላረጀውን በግ ፣ ጥርሱ ያልዘረዘረውን ንጹህ የአንድ አመት ጠቦት በግ ለእግዚአብሔር ንፁህ መሥዋዕት አቀረበ።

ልጆች እግዚአብሔር ጥሩ ሥራን ስለሚወድ ወደ አቤልና ወደ መሥዋዕቱ ተመለከተ። ነገር ግን ቃየል ጥሩ ሥራ ስላልሰራ ወደ ቃየልና ወደ መሥዋዕቱ አልተመለከተም። በዚህም ምክንያት ቃየል እጅግ ተናደደ ፊቱም ጠቆረ። እግዚአብሔርም ቃየል አለው ለምን ተናደድህ? ለምንስ ፊትህ ጠቆረ? መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት ንብል፣ ቅጣትም ይጠብቅሃል

Read more

ወወሃብኮሙ ትእምርት ለእለ ይፈርሁከ፣ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው (መዝ 59፡4)

በመምህር ሰሎሞን መኩሪያ

መስከረም  16 ቀን 2006 ዓ.ም.

ይህንን የተናገረ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ነው፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ከተሰጡት 7 ሃብታት አንዱ ሃብትንቢት  ነው በዚተሰጠው ሃብ ትንቢት  የራቀው ቀርለታል የቀረበው ከናውኖለታልየረቀቀው ጐልቶለታል ስለዚህም ከእርሱ በፊት የተደረገውን፣ በእርሱ ዘመን የሆነውን፣ ከእርሱም በኋላ እስከ እለተ ምፅአት የሚደረገውን ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር ገልፆለት ብዙ ነገር ተንብይዋል። ትንቢቶቹም መካከል አንዱ የመስቀሉ ነገር ነው፡፡

ቅዱስ መስቀል እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውሃ ፈሳሽ  ሳይሆን ትንቢት ሲነገርለት ምሳሌ ሲመሰልለት የኖረና በኃላም በከበረ በክርስቶስ ደም ተቀድሶ የመለኮት ዙፋን ሆኖ የተመረጠ ለክርስቲያኖች ኃይልና መመኪያ እንዲሁም አጋንንትን ድል መንሻ ነው፡፡

Read more

አዳም እና ሔዋን (ለልጆች) (ዘፍ 1፣2፣3)

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች?

በአለፈው በቀረበው ክፍለ ትምህርት እግዚአብሔር ለፈጠራቸው ፍጥረታት እንዳነበባችሁና እንደተረዳችሁ ተስፋ እናደርጋለን። በዚህ ጽሑፍ ደግሞ እግዚአብሔር በስድስተኛው ቀን ለፈጠራቸው አዳም እና ሔዋን እንደሚከተለው ቀርቦላችኋል።

እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ኑሮ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ከፈጠረለት በኋላ በስድስተኛው ቀን ዐርብ የመጀመርያውን ሰው አዳምን ፈጠረ። እግዚአብሔር ሲፈጥረውም በእራሱ መልክ እና ምሳሌ ፈጠረው፤ በምድር ላይ ለሚኖሩ ፍጥረታት ሁሉ ገዢ አደረገው። እግዚአብሔርምአዳም ብቻውን በመሆኑ ከጎኑ አጥንትን ወስዶ ሔዋንን ፈጠራት። በተፈጠሩበት ምድር አዳም አርባ ቀን ፣ ሔዋን ደግሞ ሰማንያ ቀን ከቆዩ በኋላ ወደ ኤዶም ገነት አስገባቸው። ይህን መሠረት አድርጋ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወንዶች በተወለዱ በአርባ ቀናቸው ፣ ሴቶች በተወለዱ በሰማንያ ቀናቸው ተጠምቀው የእግዚአብሔር ልጆች እንዲሆኑ ታደርጋለች።

Read more

ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ፤ በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፤ (መዝ 64፥ 11)

/  ውብዓለም  ደስታ 

ጳጉሜን 04 ቀን 2005 ዓ.ም. 

ዘመን የሚለወጥበት የመስከረም ወር ዘር ዘርተው ተክል ተክለው የሚኖሩ ሐረስተ ምድር በክረምት የዘሩትን ዘር አሽቶ አፍርቶ ምድርም በልምላሜ ተጊጣ እንስሳትም ለምለሙን ሣር ግጠው ጽሩውን ውኃ ተጎንጭተው ጠግበው አምረው የሚታዩበት የልምላሜ የፍሬ ወር ነው። “ምድርን ጐበኘሃት አጠጣሃትም፥ ብልጥግናዋንም እጅግ አበዛህ፤ የእግዚአብሔርን ወንዝ ውኃን የተመላ ነው፤ ምግባቸውን አዘጋጀህ እንዲሁ ታሰናዳለህና። ትልምዋን ታረካለህ፥ ቦይዋንም ታስተካክላለህ፤ በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ፥ ቡቃያዋንም ትባርካለህ። በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ፥ ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ። ማሰማርያዎች መንጎችን ለበሱ፥ ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ፤ በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉም” እንዳለ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ። መዝ (64 (65)፥ 9-13)

Read more

“ወደጄ ሆይ ተነሺ፣ ውበቴ ሆይ ነይ” (መኃ 2፡10)

ዲ/ን ውብዓለም ደስታ 

ከኔዘርላንድስ ቀጠና ማዕከል 

ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም. 

wodaje hoy tenesh

 ከላይ በርዕሱ እንደተገለጸው ከመዝሙር ሁሉ በሚበልጥ መዝሙሩ ሰሎሞን እመቤታችንን እንዲህ ብሏታል፡፡ «ወደጄ ሆይ ተነሺ፣ ውበቴ ሆይ ነይ፡፡ እነሆ ክረምት አለፈ ÷ ዝናቡም አልፎ ሄደ ፤ አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ፣ የዜማም ጊዜ ደረሰ ÷ የቁርዬውም ቃል በምድራችን ተሰማ፡፡ በለሱ ጎመራ ወይኖችም አበቡ መዐዛቸውንም ሰጡ ወዳጄ ሆይ ተነሺ፤ ውበቴ ሆይ ነይ፡፡» (መኃ.2-10-14)፡፡ ይህ ኃይለ ቃል ሲተረጎም በውስጡ ብዙ ምስጢራዊ ነገሮችን ያቀፈ ነው፡፡ «በክረምትና በዝናብ» የተመሰሉ የእመቤታችን መከራዎች ናቸው፡፡ የመከራሽ ጊዜ አልፏል ሲላት «አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ» ማለቱ ከልጅሽ እግር ሥር ቁጭ ብለው ተምረው ወንጌልን የተቀበሉ ሐዋርያት አንቺን በእናትነት የተረከቡ የሐዋርያት ድምፅ ወይም ስብከት በምድር ሁሉ መሰማቱን ያጠይቃል፡፡

Read more